ባይኑ ቀለም ሰበብ
የታሰረ ጓዴን ልጎበኘው ሄጄ
"እስር ቤት እንዴት ነው?" ስለው ለወዳጄ
እንዲህ አለኝ ልጄ ...
" እስር ምንም አይል
ነፃነትን ገፎ ነፃነት ያለብሳል
ትንሽ አስረስቶ ትልቁን ያስመኛል።
ይልቅ ልጠይቅህ...
ትልቁ እስር ቤት በቃ ተመቻችሁ?
በ'ዛ ክፍት ጣሪያው
ፀሐይ እና ዶፉን ሲያዘንብባችሁ
ሲሳይ መሰላችሁ? "
ሰኞ 27 ኦክቶበር 2014
ረቡዕ 22 ኦክቶበር 2014
ግር
ልክ እንደ በግ መንጋ
ግር ብለው መጥተው
መስኩን ግጠው ግጠው
አፈሩን ለንፋስ
አለቱን ለፀሐይ
አሳልፈው ሰጥተው
በመጡበት ብሂል
ግር ብለው ሊሄዱ
ድንገት ሲሰናዱ
ግር ይላል መንገዱ።
ግር ብለው መጥተው
መስኩን ግጠው ግጠው
አፈሩን ለንፋስ
አለቱን ለፀሐይ
አሳልፈው ሰጥተው
በመጡበት ብሂል
ግር ብለው ሊሄዱ
ድንገት ሲሰናዱ
ግር ይላል መንገዱ።
ማክሰኞ 21 ኦክቶበር 2014
ጥፋት
ትናንትናችንን - ካጋባስንበት የታሪክ ረብጣ
ዛሬያችንን - ከቸረቸርነው ለእለት ቂጣ
ነገአችንን - ከተበደርነው ባ'ራጣ
ለ'ኛ ካለ'ኛ - ማን አለን አጥፊ ባላንጣ።
ዛሬያችንን - ከቸረቸርነው ለእለት ቂጣ
ነገአችንን - ከተበደርነው ባ'ራጣ
ለ'ኛ ካለ'ኛ - ማን አለን አጥፊ ባላንጣ።
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
ልጥፎች (Atom)