የብርሃኑ ስንኞች
የስነ-ግጥም ጦማር
Home
About
ማክሰኞ 5 ኦገስት 2014
መሃረቤን
"መሃረቤን ያያችሁ"
ብዬ ሳጫውታችሁ
"አላየንም" ላላችሁ
ሄድኩኝ እዛው ትቻችሁ።
መሃረብ ልሸምት ወጣሁ
ገበያዉን አዳረስሁ
ብዞር ከጫፍ እስከ ጫፍ
ተወዷል መሃረብ እንደ ጤፍ።
"ለምን?" ብዬ ብጠይቅ
ይመልሳል ባለሱቅ
መሀረብ የተወደደው
ዋጋው ሰማይ የነካው
ብልፅግና ኮርኩሮት፣
እንባው "አልቆምም!" ያለው
በሳቅ የሚያነባ፣
ሸማች ስለበዛ ነው።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ
በጣም አዲስ ልጥፍ
የቆየ ልጥፍ
መነሻ
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
አስተያየቶች ለጥፍ (Atom)
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ