እንደማነባ ቀድመው አውቀው
ለልቅሶዬ ደህንነት ተጨንቀው
ሾሙልኝ እንባ ጠባቂ
ላያስጥለኝ ከነጣቂ።
ሰኞ 16 ማርች 2015
አቤቱ
የፍርሃቴ ዝንበት ፍጥነቱ
ከካፊያ ወደ ዶፍ ምጥቀቱ
የድፍረቴ ጤዛነቱ
በጫጉላ ጠሐይ ትነቱ
የልቤ ድምታው ድቤነቱ
ከቤተ-ደረት ማስተጋባቱ
ለግርማ ሞገስሽ ለሴትነቱ።
ከካፊያ ወደ ዶፍ ምጥቀቱ
የድፍረቴ ጤዛነቱ
በጫጉላ ጠሐይ ትነቱ
የልቤ ድምታው ድቤነቱ
ከቤተ-ደረት ማስተጋባቱ
ለግርማ ሞገስሽ ለሴትነቱ።
እሑድ 1 ማርች 2015
የዜግነት ነገር
እኔስ ብዬ ነበር፣
ዓለም ናት ሃገሬ
የሰው ዘር ነው ዘሬ
ወንዛ ወንዙ ወንዜ ፣ ሰፈሩ ሰፈሬ።
እኔስ ብዬ ነበር፣
ስፍሩ ነው ስፍሬ
ቁጥሩ ነው ቁጥሬ።
እኔስ ብዬ ነበር፣
አርቆ ላጤነው ፣ ከቅዥት ባሻገር
ሕልሜ ድንበር-የለሽ ፣ አድማስ'ሚሻገር።
እኔስ ብዬ ነበር ፣ ሰው ሁሉ ያገሬ ልጅ
ማጀቱ ማጀቴ ፣ ደጃፉ ለኔም ደጅ።
ካለም ተነጥዬ ፣ ካገር እንድረጋ
ሳልወድ ለጠፉብኝ ፣ ፓስፖርት ይሉት ታርጋ
ብጎመዥ ብቋምጥ ፣ ላልሆን ያለም ዜጋ።
ዓለም ናት ሃገሬ
የሰው ዘር ነው ዘሬ
ወንዛ ወንዙ ወንዜ ፣ ሰፈሩ ሰፈሬ።
እኔስ ብዬ ነበር፣
ስፍሩ ነው ስፍሬ
ቁጥሩ ነው ቁጥሬ።
እኔስ ብዬ ነበር፣
አርቆ ላጤነው ፣ ከቅዥት ባሻገር
ሕልሜ ድንበር-የለሽ ፣ አድማስ'ሚሻገር።
እኔስ ብዬ ነበር ፣ ሰው ሁሉ ያገሬ ልጅ
ማጀቱ ማጀቴ ፣ ደጃፉ ለኔም ደጅ።
ካለም ተነጥዬ ፣ ካገር እንድረጋ
ሳልወድ ለጠፉብኝ ፣ ፓስፖርት ይሉት ታርጋ
ብጎመዥ ብቋምጥ ፣ ላልሆን ያለም ዜጋ።
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
ልጥፎች (Atom)