ሐሙስ 18 ጁን 2015

ዞትር ሕያውነት

በትቢያነቱ ጊዜ፣
ከፍግ ተዳብሎ ተጣለ
ለምለም ሣር ሆኖ ከች አለ!
በሣርነቱ ዘመን፣
በጥርስ መንጋ ተጋጠ
ተመዥጎ ተሰለቀጠ
ከድቀቱ ዉርጅብኝ ፣ በሬ ሆኖ አመለጠ!
በበሬነቱ ጊዜ፣
አፈር ሲገፋ ሰነበተ
ባንዲት የቁርጥ ቀን። ታርዶ ተበለተ
አፅሙን በሥጋ ሸፍኖ ፣ ሰው ሆኖ ተከሰተ!
እሱ እቴ፣
ሰርክ ኗሪነቱ እየደረጀ
ላዲስ ህይወቱ ጥርጊያ መንገድ እያበጀ
ዞትር ይመጣል ሄደ ሲሉት
በገደብ አልባ ሕያውነት።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ