በትቢያነቱ ጊዜ፣
ከፍግ ተዳብሎ ተጣለ
ለምለም ሣር ሆኖ ከች አለ!
በሣርነቱ ዘመን፣
በጥርስ መንጋ ተጋጠ
ተመንዥጎ ተሰለቀጠ
ከድቀቱ ዉርጅብኝ ፣ በሬ ሆኖ አመለጠ!
በበሬነቱ ጊዜ፣
አፈር ሲገፋ ሰነበተ
ባንዲት የቁርጥ ቀን። ታርዶ ተበለተ
አፅሙን በሥጋ ሸፍኖ ፣ ሰው ሆኖ ተከሰተ!
እሱ እቴ፣
ሰርክ ኗሪነቱ እየደረጀ
ላዲስ ህይወቱ ጥርጊያ መንገድ እያበጀ
ዞትር ይመጣል ሄደ ሲሉት
በገደብ አልባ ሕያውነት።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ