ሐሙስ 15 ኦክቶበር 2015

በምን ብልሃት

ከበራፍሽ ፈፋ
ፊትሽ ሳልደፋ
እንዳደይ አበባ
ሆ ብዬ ሳልገባ
እንደ ደራሹ ጎርፍ
ክንፌን ጥዬ ሳልከንፍ
እንደ ዲታ አፍቃሪ
ሳያሻኝ መስካሪ
መኖሬ ተጋርዶ ፣ በዚህ ሁሉ አማላይ
እንዴት ዉብ አይኖችሽ ፣ አረፉ ከእኔ ላይ።