ረቡዕ 19 ፌብሩዋሪ 2014

ካንቺ ጋራ

ደማቅ ከዋክብት ፣ ከልባቸው እየሳቁ
እኔና እንቺን ብቻ ፣ በደስታ ሲያጠምቁ
ጨረቃዋም ፣ ፈክታ በተራዋ
ስታስጌጠን ፣ በጣፋጭ ፈገግታዋ
በፍቅርሽ ምትሃት ፣ ተዘውሬ
ብቅ እላለሁ ፣ እንደገና ተፈጥሬ።

አንድም ቃል ፣ ካንደበታችን ስይወጣ
ጮክ ብለን ስናወጋ ፣ ፍፁም በፀጥታ
ፈውሰ-ፍቅርሽ ፣ በደሜ ናኝቶ
ህመም መከራዬን አሰናብቶ
የጊዜ ዑደት፣ ሕጉ ላልቶ
ያሳለፍናቸው ፣ እልፍ ቀናት
ያጥሩብኛል ፣ እንደ ቅፅበት
አይን ጨፍኖ ፣ እንደመክፈት።



ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ