ዓርብ 16 ሜይ 2014

የቸገረ ነገር

ያብሮነት ሲሆን መዝሙሩ፤
ክርሮ ከተወጠረ ደም-ሥሩ፤
የብርሃን ጎዳና ስትጠቁመው፤
የፅልመት ጉራንጉር ከዋጠው፤
አይኑ እያየ የሰው ምስል፤
ልቡ ክፉ አዉሬ ሲስል፤
ባንድነት አልጋ ተተኝቶ፣
በልዩነት ደወል ከተነቃ፤
ዛሬን ማለፍ ዳገት ሆኖ፣
ነገም ዘበት ሆነ በቃ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ