ዓርብ 6 ጁን 2014

ቢቸግረኝ

በሰው መንጋ ተከብቤ
እውነት ሲሆን ጥሜ ራቤ
የሀቅ ልሳን ግቷ ነጥፎ
ክህደት ሲያዳፋኝ ጠልፎ
በቅጥፈት ጥላሸት ተለቅልቄ፣
በብቸኝነት ስለከሰልኩ
ዋሾ ወዳጄን ሸኝቼ፣
ታማኝ ባላንጣዬን ተቀበልኩ።

ሐሙስ 5 ጁን 2014

የበላኝ ጅብ

ሳያማትር ዙርያ ገባውን፤
ሳያደምጥ የገዛ ጆሮዉን፤
ባንክሮ አቀርቅሮ ከዘንጠለ፤
ሲጠሩት "አቤት" ካላለ፤
ድምፅ ፣ ትንፋሹን አምቆ፤
ጥላ ፣ ኮቴዉን ደብቆ፤
የበላኝ ጅብ ፀጥ ካለ፤
ከሁለት አንድ ነገር አለ...
ወዲህም ላይጠራ ቢጤዉን፤
ወዲያም ባይሞላ ስልቻውን።