ሐሙስ 5 ጁን 2014

የበላኝ ጅብ

ሳያማትር ዙርያ ገባውን፤
ሳያደምጥ የገዛ ጆሮዉን፤
ባንክሮ አቀርቅሮ ከዘንጠለ፤
ሲጠሩት "አቤት" ካላለ፤
ድምፅ ፣ ትንፋሹን አምቆ፤
ጥላ ፣ ኮቴዉን ደብቆ፤
የበላኝ ጅብ ፀጥ ካለ፤
ከሁለት አንድ ነገር አለ...
ወዲህም ላይጠራ ቢጤዉን፤
ወዲያም ባይሞላ ስልቻውን።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ