በሰጠምኩኝ መጠን ስንሳፈፍ
ከመናፍቅነት ገለባ ተበጥሬ ሳልፍ
ገላየ በልብ ከልብ ቀልጦ
ልቤ ከነፍስ ባህር ሰምጦ
ነፍሴ በፍቅር ቅመም ተላቁጦ
ገላዬ ማሳ ሆኖለት
ህመሜ ተዘራ ታጨደ
መድሃኒት ብዬ የዋጥኩት
ማዳበሪያ ሆኖለት ቀለደ።
ቅዳሜ 30 ጃንዋሪ 2016
ዋጋ
ሰርቆ ሳሚ ሲመጣ፣ ተይው በብላሽ ይላስሽ
የኔ ተራ ሲሆን ግን፣ ዋጋው ይናር ከንፈርሽ
ወሮ በላን ስትከሽው፣ ይቅር በይው ለምነትሽ
የኔ ወንጀል ሲሆን ግን፣ አይቀጡ ቅጣት ይኑርሽ።
የኔ ተራ ሲሆን ግን፣ ዋጋው ይናር ከንፈርሽ
ወሮ በላን ስትከሽው፣ ይቅር በይው ለምነትሽ
የኔ ወንጀል ሲሆን ግን፣ አይቀጡ ቅጣት ይኑርሽ።
አታሚ
ብቻዬን ከብቸኘት ስታገል
ፍርሃቴ ፍም አውጥቶ ሲንበለበል
ያ የስንብት አዋጅሽ
ያ የ "ደህና ሁን" ፍርድሽ
ልክ እንዳላዩት ሩቅ ሀገር
እንዳልገለጡት መፅሐፍ
እንዳልጠገኑት ሰባራ ልብ
እንዳላበሱት የንባ ዘለላ
ሰርክ የናፍቆት ጌሾ ነው፣
ዘሎ ፊጥ 'ሚል ከራሴ
ዞትር የቁጭት ጅራፍ ነው፣
ሰንበር አታሚ ከመንፈሴ።
ፍርሃቴ ፍም አውጥቶ ሲንበለበል
ያ የስንብት አዋጅሽ
ያ የ "ደህና ሁን" ፍርድሽ
ልክ እንዳላዩት ሩቅ ሀገር
እንዳልገለጡት መፅሐፍ
እንዳልጠገኑት ሰባራ ልብ
እንዳላበሱት የንባ ዘለላ
ሰርክ የናፍቆት ጌሾ ነው፣
ዘሎ ፊጥ 'ሚል ከራሴ
ዞትር የቁጭት ጅራፍ ነው፣
ሰንበር አታሚ ከመንፈሴ።
ክፋቱ
ጨለማው ፍፁም ሳይፀልም
ብርሃኑም እጅግ ሳይለመልም
በተስፋ ነበልባል በእምነት
በጥርጣሬ ሰይፍ በፍርሃት
ስለመንደዱ ስለመድማቱ
ልብ ልብ አለማለቱ
ዘግይቶ ማወቅ ክፋቱ።
ብርሃኑም እጅግ ሳይለመልም
በተስፋ ነበልባል በእምነት
በጥርጣሬ ሰይፍ በፍርሃት
ስለመንደዱ ስለመድማቱ
ልብ ልብ አለማለቱ
ዘግይቶ ማወቅ ክፋቱ።
ኩ!
ቱግ ብዬ ተንተክትኬ
ከቆምኩበት ተፈትልኬ
ወረድኩኝ ከወንዛ ወንዙ
ሰከንኩኝ ካፍ ከገደፉ
ብለኩሰው አይበራ
ብደግፈው አይጠና
ብቆሰቁሰው ተዳፍኖ
ብኮተኩተው መንምኖ
ያሳብ ጠኔ ደልቆኝ
ያንጎል አፅሜን አድቅቆኝ
በደራሽ ድፍረት ተሞልቼ
ያሳብ ብስናዬን አግስቼ
ተወርውሬ ከዉሃው እንዳረፍኩ
እግዚኦ ከምኔው ሰጠምኩ
አበስኩ!
ገበርኩ!
ከቆምኩበት ተፈትልኬ
ወረድኩኝ ከወንዛ ወንዙ
ሰከንኩኝ ካፍ ከገደፉ
ብለኩሰው አይበራ
ብደግፈው አይጠና
ብቆሰቁሰው ተዳፍኖ
ብኮተኩተው መንምኖ
ያሳብ ጠኔ ደልቆኝ
ያንጎል አፅሜን አድቅቆኝ
በደራሽ ድፍረት ተሞልቼ
ያሳብ ብስናዬን አግስቼ
ተወርውሬ ከዉሃው እንዳረፍኩ
እግዚኦ ከምኔው ሰጠምኩ
አበስኩ!
ገበርኩ!
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
ልጥፎች (Atom)