ቅዳሜ 30 ጃንዋሪ 2016

አታሚ

ብቻዬን ከብቸኘት ስታገል
ፍርሃቴ ፍም አውጥቶ ሲንበለበል
ያ የስንብት አዋጅሽ
ያ የ "ደህና ሁን" ፍርድሽ
ልክ እንዳላዩት ሩቅ ሀገር
እንዳልገለጡት መፅሐፍ
እንዳልጠገኑት ሰባራ ልብ
እንዳላበሱት የንባ ዘለላ
ሰርክ የናፍቆት ጌሾ ነው፣
ዘሎ ፊጥ 'ሚል ከራሴ
ዞትር የቁጭት ጅራፍ ነው፣
ሰንበር አታሚ ከመንፈሴ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ