ቅዳሜ 30 ጃንዋሪ 2016

የተቃርኖ ማማ

በሰጠምኩኝ መጠን ስንሳፈፍ
ከመናፍቅነት ገለባ ተበጥሬ ሳልፍ
ገላየ በልብ ከልብ ቀልጦ
ልቤ ከነፍስ ባህር ሰምጦ
ነፍሴ በፍቅር ቅመም ተላቁጦ
ገላዬ ማሳ ሆኖለት
ህመሜ ተዘራ ታጨደ
መድሃኒት ብዬ የዋጥኩት
ማዳበሪያ ሆኖለት ቀለደ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ