ዓርብ 22 ኤፕሪል 2016

ምሽት ነበር

የኦሪዮን ክዋክብቱ፣
ርጌልና ቤቴልጌስ፣
ነጥተው ገዝፈው የቀሉበት
ምሽት ነበር፣ዉድ ምሽት
ዋጋው ካልማዝ ከ'ንቁ በላይ
ከፊቴና ከፊትሽ ላይ
ወዙ ደምቆ ፈክቶ ሚታይ።
ምሽት ነበር አይረሴ፣ ተስፋው ከማር የጣፈጠ
ለመግባባት ስንታገል፣ ሳንጨብጠው ያመለጠ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ