ዓርብ 22 ኤፕሪል 2016

አይገርምሽም?

ድልድዩ ዋዣቂ፣
ካለት ሲያነክተን
ወንዙም ችኩል ደራሽ፣
ከግንድ ሲያላትመን
ባሕሩም ሞገደኛ፣
መርከብ ሲያስታቅፈን...
ህዋስሽ ህዋሴ፣
ነፍስሽና ነፍሴ፣
በዉዥንብር ናዳ፣ ሲልሙ ሲደቅቁ
አይገርምሽም ዉዴ፣
ቃልሽ ከቃሌ ጋር፣ እንዲህ መጣበቁ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ