ረቡዕ 22 ፌብሩዋሪ 2017

ምኑን

ኡኡታ ካስመነጠረ 
ዝምታ ካስጠረጠረ
ዋቲው በተድላ ካልዋለ
ማቲው በረካ ካላደረ
የመጠላለፍ ፈንጣጣ 
ባ'ጋርነት ጠበል ልፍልፎ ካልወጣ 
የ'ንባ ተራራ ካልተናደ 
 የበደል መጋረጃ ካልተቀደደ 
መዥገሮች ከትከሻ ካልወረዱ 
ዳኞች በሀቅ ካልፈረዱ 
 ገበታው ካልቀረበ ያለስጋት 
ወጉ ካልተወጋ ያለፍርሃት
ምኑን አዲስ ቀን መጣ 
ምኑን አደይ ፈነዳ 
ምኑን አየን አበባ 
ምኑን መስከረም ጠባ!

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ