ታልቀረ መመኘት
ተመኘሁ ዛፍነት
ከላዬ አራግፌ ፣ ጥውልግ ቅጠሎቼን
ቅርንጫፎቼ አድገው ፣ አጠንክሬው ግንዴን
እንዳዲስ ፀድቄ ፣ ለምልሜ ዳግመኛ
ለቅዥቴ ሳይሆን ፣ ለህልሜ እንድተኛ።
ረቡዕ 26 ኖቬምበር 2014
ቅዳሜ 22 ኖቬምበር 2014
አውቃለሁ
እርግጥ ነው በድዬሻለሁ
እውነት ነው ጎድቼሻለሁ
ሁሉንም ጠንቅቄ አውቃለሁ።
በናፍቆት ሰቀቀን
በመገፋት ቆፈን
እንደማለዳ ዉርጭ እንሰፍስፌሻለሁ።
አውቃለሁ።
ዱካዬን አጥፍቼ በፈለግሽኝ ጊዜ
ሰው አልባ አድርጌሽ በወንዝሽ በወንዜ
እንደቆላ ሃሩር አጠውልጌሻለሁ።
ይህንንም አውቃለሁ።
ሆኘ ያልሁንሁትን
ኖሮኝ የሌለኝን
በቁሜ ስቃዥ በቀን
ክፉ ህልምሽ ሆኘ እንቅልፍሽን ነጥቄሻለሁ።
ይህንንም አውቃለሁ።
ዳብሼ ሌላ ገላ
ጎርሼ ሌላ ከንፈር
በቅናት ማዕበል አናውጬ አዳፍቼሻለሁ
ከሰው ተራ አሽቀንጥሬ ወርዉሬሻለሁ
ከመሃል ጎተቼ ወደ ዳር ገፍቼሻለሁ
ከንፈርሽን በጥርሶችሽ አስነከሼሻለሁ።
ይህንንም አውቃለሁ።
እቶን ወላፈኑ ከሩቅ በሚንቦገቦገው
በበደል ምጣድ ላይ አገላብጨሻለሁ
አሻሮ እስኪወጣሽ እስክታሪ አምሼሻለሁ
ይህንንም አውቃለሁ።
እርግጥ ነው በድዬሻለሁ
እውነት ነው ጎድቼሻለሁ
ሁሉንም ጠንቅቄ አውቃለሁ።
ዉስጥሽ ግን እንዲህ ሲል ሰማለሁ...
ከበደል ከስቃይ ከበቀል ባሻገር
እጅ ባፍ 'ሚያስጭን የረቀቀ ምሥጢር
በልብ የሚዳሰስ ከስሜት ጥላ ስር
ምህረት አይገደዉም እውነተኛ ፍቅር።
እውነት ነው ጎድቼሻለሁ
ሁሉንም ጠንቅቄ አውቃለሁ።
በናፍቆት ሰቀቀን
በመገፋት ቆፈን
እንደማለዳ ዉርጭ እንሰፍስፌሻለሁ።
አውቃለሁ።
ዱካዬን አጥፍቼ በፈለግሽኝ ጊዜ
ሰው አልባ አድርጌሽ በወንዝሽ በወንዜ
እንደቆላ ሃሩር አጠውልጌሻለሁ።
ይህንንም አውቃለሁ።
ሆኘ ያልሁንሁትን
ኖሮኝ የሌለኝን
በቁሜ ስቃዥ በቀን
ክፉ ህልምሽ ሆኘ እንቅልፍሽን ነጥቄሻለሁ።
ይህንንም አውቃለሁ።
ዳብሼ ሌላ ገላ
ጎርሼ ሌላ ከንፈር
በቅናት ማዕበል አናውጬ አዳፍቼሻለሁ
ከሰው ተራ አሽቀንጥሬ ወርዉሬሻለሁ
ከመሃል ጎተቼ ወደ ዳር ገፍቼሻለሁ
ከንፈርሽን በጥርሶችሽ አስነከሼሻለሁ።
ይህንንም አውቃለሁ።
እቶን ወላፈኑ ከሩቅ በሚንቦገቦገው
በበደል ምጣድ ላይ አገላብጨሻለሁ
አሻሮ እስኪወጣሽ እስክታሪ አምሼሻለሁ
ይህንንም አውቃለሁ።
እርግጥ ነው በድዬሻለሁ
እውነት ነው ጎድቼሻለሁ
ሁሉንም ጠንቅቄ አውቃለሁ።
ዉስጥሽ ግን እንዲህ ሲል ሰማለሁ...
ከበደል ከስቃይ ከበቀል ባሻገር
እጅ ባፍ 'ሚያስጭን የረቀቀ ምሥጢር
በልብ የሚዳሰስ ከስሜት ጥላ ስር
ምህረት አይገደዉም እውነተኛ ፍቅር።
ሰኞ 17 ኖቬምበር 2014
ረቡዕ 12 ኖቬምበር 2014
ባመድ አፋሹ እጅሽ
ያኔ፣
የጎረሱትን አላምጠው ፣ አጣጥመው ሳይዉጡ
ያጎረሳቸዉን እጅሽን ፣ መልሰው ሊንከሱ ሲሮጡ
ፊትሽ በምሬት ከስሎ ፣ ገር እንጀትሽ እያረረ
ሀቀኛው እንደበትሽ ፣ ተከፍቶ እያማረረ
"እጄ አመድ አፋሽ ነው" ብለሽ ነግረሽን ነበረ።
ዛሬ፣
ባንቺው ቅጥ-አጥ ቅጥፈት ፣ ጅስሚያችንን ካበገንሽው
የመንደዳችንን ነበልባል ፣ ለቆፈንሽ ማክሰሚያ ከሞቅሽው
አደራ ንፋስ ሳይቀድምሽ ፣ አመዳችንንም እፈሽው
የጎረሱትን አላምጠው ፣ አጣጥመው ሳይዉጡ
ያጎረሳቸዉን እጅሽን ፣ መልሰው ሊንከሱ ሲሮጡ
ፊትሽ በምሬት ከስሎ ፣ ገር እንጀትሽ እያረረ
ሀቀኛው እንደበትሽ ፣ ተከፍቶ እያማረረ
"እጄ አመድ አፋሽ ነው" ብለሽ ነግረሽን ነበረ።
ዛሬ፣
ባንቺው ቅጥ-አጥ ቅጥፈት ፣ ጅስሚያችንን ካበገንሽው
የመንደዳችንን ነበልባል ፣ ለቆፈንሽ ማክሰሚያ ከሞቅሽው
አደራ ንፋስ ሳይቀድምሽ ፣ አመዳችንንም እፈሽው
ሐሙስ 6 ኖቬምበር 2014
ተከልሎ ላይከለል
በሕመማችን ልክ ፣ ደዌዉን ለሚያፀዳ
በጥማታችን መጠን ፣ ወይን ጠጁን ለሚቀዳ
በጠኔያችን ስፍር ፣ ለሚቆርጥ ፍሪዳ
ላዛኝ ቅቤ አንጉዋቹ ፣ ለባዕድ እንግዳ
ገመና ሊከለል ፣ መንገዱ ቢፀዳ
ዛፉ ሳር ቅጠሉ ፣ ቢመስል ፀአዳ
ያ'ፍታ እድፍ እንጂ ፣ ችግር ላይፀዳ
...
ፍስሃን ደስኩሮ ፣ እንደሄደ እንግዳው
በተማፅኖ ትእይንት ፣ ይደምቃል ጎዳናው
ባ'ዳፋ ደግ እጆች
ባ'ሳዛኝ ዉብ አይኖች
በ'ውነተኛዎቹ ፣ የህላዌ መልኮች
በመሰንበት ትግል ፣ ሕያ ምስክሮች።
በጥማታችን መጠን ፣ ወይን ጠጁን ለሚቀዳ
በጠኔያችን ስፍር ፣ ለሚቆርጥ ፍሪዳ
ላዛኝ ቅቤ አንጉዋቹ ፣ ለባዕድ እንግዳ
ገመና ሊከለል ፣ መንገዱ ቢፀዳ
ዛፉ ሳር ቅጠሉ ፣ ቢመስል ፀአዳ
ያ'ፍታ እድፍ እንጂ ፣ ችግር ላይፀዳ
...
ፍስሃን ደስኩሮ ፣ እንደሄደ እንግዳው
በተማፅኖ ትእይንት ፣ ይደምቃል ጎዳናው
ባ'ዳፋ ደግ እጆች
ባ'ሳዛኝ ዉብ አይኖች
በ'ውነተኛዎቹ ፣ የህላዌ መልኮች
በመሰንበት ትግል ፣ ሕያ ምስክሮች።
ሰኞ 3 ኖቬምበር 2014
ዘመኑን ለገደለ
በስንፍና ጠብ-መንጃው ፣ አቀባብሎ እያለመ
ምትክ-አልባ ዘመኑን ፣ አከታትሎ ላጋደመ
ጅብዱዉን ቆሞ ቢተርክ ፣ <<ካለ'ኔ ጀግና>> እያለ
ቁልቁል በሚያየው ግዳይ ዉስጥ ፣ እልፍ የራሱ ሞት አለ።
ምትክ-አልባ ዘመኑን ፣ አከታትሎ ላጋደመ
ጅብዱዉን ቆሞ ቢተርክ ፣ <<ካለ'ኔ ጀግና>> እያለ
ቁልቁል በሚያየው ግዳይ ዉስጥ ፣ እልፍ የራሱ ሞት አለ።
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
ልጥፎች (Atom)