ሰኞ 3 ኖቬምበር 2014

ዘመኑን ለገደለ

በስንፍና ጠብ-መንጃው ፣ አቀባብሎ እያለመ
ምትክ-አልባ ዘመኑን ፣ አከታትሎ ላጋደመ
ጅብዱዉን ቆሞ ቢተርክ ፣ <<ካለ'ኔ ጀግና>> እያለ
ቁልቁል በሚያየው ግዳይ ዉስጥ ፣ እልፍ የራሱ ሞት አለ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ