ሐሙስ 6 ኖቬምበር 2014

ተከልሎ ላይከለል

በሕመማችን ልክ ፣ ደዌዉን ለሚያፀዳ
በጥማታችን መጠን ፣ ወይን ጠጁን ለሚቀዳ
በጠኔያችን ስፍር ፣ ለሚቆርጥ ፍሪዳ
ላዛኝ ቅቤ አንጉዋቹ ፣ ለባዕድ እንግዳ
ገመና ሊከለል ፣ መንገዱ ቢፀዳ
ዛፉ ሳር ቅጠሉ ፣ ቢመስል ፀአዳ  
ያ'ፍታ እድፍ እንጂ ፣ ችግር ላይፀዳ
...
ፍስሃን ደስኩሮ ፣ እንደሄደ እንግዳው
በተማፅኖ ትእይንት ፣ ይደምቃል ጎዳናው
ባ'ዳፋ ደግ እጆች
ባ'ሳዛኝ ዉብ አይኖች
በ'ውነተኛዎቹ ፣ የህላዌ መልኮች
በመሰንበት ትግል ፣ ሕያ ምስክሮች።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ