ያኔ፣
የጎረሱትን አላምጠው ፣ አጣጥመው ሳይዉጡ
ያጎረሳቸዉን እጅሽን ፣ መልሰው ሊንከሱ ሲሮጡ
ፊትሽ በምሬት ከስሎ ፣ ገር እንጀትሽ እያረረ
ሀቀኛው እንደበትሽ ፣ ተከፍቶ እያማረረ
"እጄ አመድ አፋሽ ነው" ብለሽ ነግረሽን ነበረ።
ዛሬ፣
ባንቺው ቅጥ-አጥ ቅጥፈት ፣ ጅስሚያችንን ካበገንሽው
የመንደዳችንን ነበልባል ፣ ለቆፈንሽ ማክሰሚያ ከሞቅሽው
አደራ ንፋስ ሳይቀድምሽ ፣ አመዳችንንም እፈሽው
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ