ማክሰኞ 18 ኦገስት 2015

አንዳንድ ቀን

እንዳንድ ቀን አለ፣
ምናብን እንዳክናፍ ፣ በሰፊ አዘርግቶ
ብረር ብረር ሚል ፣ ከምድር አስነስቶ።

ደሞ አለ አንዳንድ ቀን፣
ቢሆንን ሚያስመኝ ዘላለም አንድ ቀን
ጠራርጎ የሚሸኝ የ'ላዌን ሰቀቀን።

አንዳንድ ቀን አለ፣
ሳይጠሩት አቤት ባይ
ሳይልኩት ወዴት ባይ
ይሉትን አይሰማ ፣ ቃላባይ እንዳ'ባይ።

ደሞ አለ አንዳንድ ቀን፣
የቀን ባለቅኔ
በቆፈን ቆርብተህ ፣ ተቆራምተህ ሲያይህ
ሳጥን ሙሉ እርዛት፣ ደራርቦ ሚያለብስህ
ሌማት ሙሉ ጠኔ፣ ፈትፍቶ ሚያጎርስህ
እንጀትክን ሊያርስህ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ