የብርሃኑ ስንኞች
የስነ-ግጥም ጦማር
Home
About
ረቡዕ 8 ማርች 2017
ፍረጃ ህላዌ
ተናፍቆ ተናፍቆ፣
ሌት በቀን ሲተካ
ሞት መጥቶ ሲሰየም፣
በሕይወት መሥመር ዱካ
ሟች ሟችን አክሞ፣
ሟች ሟችን ሲያድነው
ሟች ሟችን አስታሞ፣
ሟች ሟችን ሲቀብረው
በትዉልድ ሰንሰለት፣ሰው በሰው ሲቀጠል
ለችግኝ መለምለም፣ጋሻ ዛፍ ሲቃጠል
በትርትሯ መሳ ጠብቃ መሰፋቷ
ላልጨበጥነው አልፋ ኦሜጋ አልባነቷ።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ
በጣም አዲስ ልጥፍ
የቆየ ልጥፍ
መነሻ
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
አስተያየቶች ለጥፍ (Atom)
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ