ባሩድ እንደጠበል፣ በጅምላ እየረጩ
አረም ለማቆየት፣ ቡቃያ እየቀጩ
በደም ቀይ ምንጣፍ፣ ዛሬን ቢራመዱ
ነገ ሸንጎ 'ሚቀርብ፣ ዶሴ ነው መንገዱ።
ሰኞ 30 ኦክቶበር 2017
ቢሆንም ባይሆንም
የህልማለም ድግስ፣
ህላዌን አንጥሮ፣ ቢያጠጣም ቅቤ
አዋዝቶ ቢያጎርስም፣ ክትፎን ከአይቤ
ሰው ምኑ ሞኝ ነው፣
ገር ሕልሙን ተማምኖ፣ አይተኛ በራብ-ጥም
ጉምዥት ሳይጎነጭ፣ ተስፋ ሳይቆረጥም።
ህላዌን አንጥሮ፣ ቢያጠጣም ቅቤ
አዋዝቶ ቢያጎርስም፣ ክትፎን ከአይቤ
ሰው ምኑ ሞኝ ነው፣
ገር ሕልሙን ተማምኖ፣ አይተኛ በራብ-ጥም
ጉምዥት ሳይጎነጭ፣ ተስፋ ሳይቆረጥም።
እኔን ሲዳኝ እኔ
አህያን ከጅብ ሳጣጥም
አይጥን ከድመት ሳሳስም
ዲስኩሬ በዉድ ሲያዋድድ
ፍም እሳትን ከደረቅ ጭድ
ልሣኔ ፈልጎ አቃርቦ
አራምባዉን ከቆቦ
ግና ምን አገኘኝ፣ ጎደልኩት ከራሴ
ደርሶ የሚከዳኝ፣ ጥሬ ቆይ ምላሴ።
አይጥን ከድመት ሳሳስም
ዲስኩሬ በዉድ ሲያዋድድ
ፍም እሳትን ከደረቅ ጭድ
ልሣኔ ፈልጎ አቃርቦ
አራምባዉን ከቆቦ
ግና ምን አገኘኝ፣ ጎደልኩት ከራሴ
ደርሶ የሚከዳኝ፣ ጥሬ ቆይ ምላሴ።
ረቡዕ 25 ኦክቶበር 2017
በጫጉላ ጨረቃ
የናፍቆትን ጋራ፣ አሟምተሽ ስታልፊ
የትዝታን ግርዶሽ፣ ገላልጠሽ ስትገፊ
ድካምሽን ለማከም፣ በቀኝሽ ስታርፊ
የእንቅልፍ መንኩራኩር፣ ይዞሽ ሲመነጠቅ
የህልም ሰረገላ፣ አሳፍሮሽ ሲነጠቅ
ከማረፊያሽ ልቤ፣ ሰገነት ቁጭ እንዳልሽ
ያ'እዋፍ ሕብረ-ዜማ፣ ቀስቅሶ ካነቃሽ
ይልቅ ጆሮ ስጪ፣ ለማለዳው ዜማ
አዋጅ ይዟልና፣
በኔ የሚነገር፣ ባንቺ የሚሰማ።
የትዝታን ግርዶሽ፣ ገላልጠሽ ስትገፊ
ድካምሽን ለማከም፣ በቀኝሽ ስታርፊ
የእንቅልፍ መንኩራኩር፣ ይዞሽ ሲመነጠቅ
የህልም ሰረገላ፣ አሳፍሮሽ ሲነጠቅ
ከማረፊያሽ ልቤ፣ ሰገነት ቁጭ እንዳልሽ
ያ'እዋፍ ሕብረ-ዜማ፣ ቀስቅሶ ካነቃሽ
ይልቅ ጆሮ ስጪ፣ ለማለዳው ዜማ
አዋጅ ይዟልና፣
በኔ የሚነገር፣ ባንቺ የሚሰማ።
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
ልጥፎች (Atom)