የብርሃኑ ስንኞች
የስነ-ግጥም ጦማር
Home
About
ረቡዕ 25 ኦክቶበር 2017
በጫጉላ ጨረቃ
የናፍቆትን ጋራ፣ አሟምተሽ ስታልፊ
የትዝታን ግርዶሽ፣ ገላልጠሽ ስትገፊ
ድካምሽን ለማከም፣ በቀኝሽ ስታርፊ
የእንቅልፍ መንኩራኩር፣ ይዞሽ ሲመነጠቅ
የህልም ሰረገላ፣ አሳፍሮሽ ሲነጠቅ
ከማረፊያሽ ልቤ፣ ሰገነት ቁጭ እንዳልሽ
ያ'እዋፍ ሕብረ-ዜማ፣ ቀስቅሶ ካነቃሽ
ይልቅ ጆሮ ስጪ፣ ለማለዳው ዜማ
አዋጅ ይዟልና፣
በኔ የሚነገር፣ ባንቺ የሚሰማ።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ
በጣም አዲስ ልጥፍ
የቆየ ልጥፍ
መነሻ
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
አስተያየቶች ለጥፍ (Atom)
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ