ረቡዕ 25 ኦክቶበር 2017

በጫጉላ ጨረቃ

የናፍቆትን ጋራ፣ አሟምተሽ ስታልፊ
የትዝታን ግርዶሽ፣ ገላልጠሽ ስትገፊ
ድካምሽን ለማከም፣ በቀኝሽ ስታርፊ
የእንቅልፍ መንኩራኩር፣ ይዞሽ ሲመነጠቅ
የህልም ሰረገላ፣ አሳፍሮሽ ሲነጠቅ
ከማረፊያሽ ልቤ፣ ሰገነት ቁጭ እንዳልሽ
ያ'እዋፍ ሕብረ-ዜማ፣ ቀስቅሶ ካነቃሽ
ይልቅ ጆሮ ስጪ፣ ለማለዳው ዜማ
አዋጅ ይዟልና፣
በኔ የሚነገር፣ ባንቺ የሚሰማ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ