ማክሰኞ 2 ሴፕቴምበር 2014

ዉዴ

አንቺን የሚመጥን ስጦታ ፍለጋ፣
ቁልቁለቱን ወረድሁ
አቀበቱን ወጣሁ

ወርቅ እንዳላመጣ፣
ከ'ግር እስከራስሽ እንድታጌጪበት
ካንቺ ወዲያ ላሳር ፣ በወርቅ አንጣሪነት

ጠጅ እንዳላመጣ
በአልማዝ ብርሌ ፣ ተቀድቶ 'ሚጠጣ
ካንቺ ወዲያ ጠጅ ጣይ
እንኩዋንስ ዘንድሮ ፣ ለርከርሞም አይታይ

ልቤን አንዳልሰጥሽ
የኔን ልብ የገራ ፣ አውራ ልብ የታደልሽ
ከሥጋ ነጥዬ ፣ ንፍሴን እንዳልቸርሽ
የኔ ብኩኗ ነፍስ ፣ ላንቺ 'ማትመጥንሽ

ያየሁት በሙሉ ካ'ይን 'ማይገባ ፣ የልብ 'ማያደርስ
ሆኖብኝ ልፋቴ ፣ ዉቅያኖስ በሲኒ ቀድቶ እንደመጨረስ
ቢጨንቀኝ ቢጠበኝ ፣ መስታወት ሰጠሁሽ
ራስሽን ስታዪ ፣ ድንገት ትዝ ብልሽ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ