ፅልመትን ሸኝተን ፣ ብርሃን ልናበስር
ተኮልኩለን ነበር ፣ ከትልቅ ዋርካ ስር
ከፍታን ለማየት ፣ ሲቃና አንገታችን
በዋርካው ቅጠሎች ፣ ተጋረደ አይናችን
ከዋርካው በስተላይ፣ ከጥላው ባሻገር
አድማስ ይንጣ ይጥቆር ፣ አልገባንም ነበር።
ባ'ንድ በገዳም ቀን
ባ'ንድ ክንድ አብረን
ያንን ግዙፍ ጥላ ፣ ያንን ግዙፍ ዋርካ
ገዝግዘን…
ገዝግዘን…
ከስር መሰረቱ ፣ ነቅለን ስናበቃ
ፀሐይ አሸልባ ፣ ነቅታለች ጨረቃ።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ