ወንዝ ባልዞረበት ድልድይ ስንዘረጋ
ምሰሶው ሳይጠና ደጃፍ ስንዘጋ
ለመላጣ እራስ ሚዶ ስንመትር
ለመከነ አዝመራ ነዶ ስንከምር
በለበጣ ስሌት አብሮነት ሲለካ
ምኞቴን ለፍፈህ፣ ምኞትክን አሳካ።
የብርሃኑ ስንኞች
የስነ-ግጥም ጦማር
እሑድ 4 ኖቬምበር 2018
ማክሰኞ 26 ዲሴምበር 2017
ለብርቱ ትከሾች እጅ መንሻ
"ወጡ ቀለም ሆኖ እንጀራው ብራና
ይድረሰኝ ደብዳቤ ተርቢያለሁና"
ብሉ እንዳልማለደ
ንፋስን አማላጅ፣
ጨረቃን አዋላጅ፣
አርጎ እንዳልነጎደ
ገብሬ ኢልማ ደስታ እንደዘበት ሄደ
ኦክላሆማ ሜዳን ቤት አርጎት ለመደ።
ከዴህሊ እስከ ሎንዶን
ከይፋት እስከ ዋሽንግቶን
ባሻ አሸብር ባለ ቧልቱ
ደማሙ ብእረኛ አብዬ መንግስቱ
ያለ ፕሮብሌም አርፎ መተኛቱ!
ዮሐንስም ሄደ፣ ሰፊ አድማሱን አስታቅፎን
"እስኪ እናንተ ጎዱች ተጠየቁ" ብሎን
በብቸኝነት ነበልባል እንደነደደ
ቅኔው ይፋቴ ዳኛቸዉም ነጎደ
ኡኡታ አሮበት "እምቧ በሉ" እያለ
የጉራማይሌ ሕልሙን፣ ቁጭት እየፈተለ
ዮናስ በኩርምት ሞቱ እያሳለው ተከተለ
"እግዚያአብሔር ትመስን፣ ክብሯ ይስፋ" እንዳለ።
ደበበ በምናቡ ስይፍ ክትፎኛ ተካትፎ
ገሞራው በረከትን ሼጣንኛ ተራግሞ
የዜሮን ቁጥርነት ከአልፋው ሞግቶ
እውነት ለሚያንቀው አገጭ ይዞ ግቶ
ከዑራኤል ዳገት ሽቅብ እየቃኘን
"እኔም እንደናንተ ሕያው ነበርኩ" አለን።
አያ ሙሌም ምህላዉን ታክቶ
አጅሬው ከመንበሩ መኖሩን ሞግቶ
ክልትው አለ ብቻዉን፣ አዘመራውን እንደነዛ
በሱ የደም ጠብታ፣ የስንቱን ግንባር ሊያወዛ።
ከአባ ገዳ ኢልማ ገልማ
የማይድን በሽታ ነፍሱ አስታማ
ከመርካቶ እስከ ኮምፔሽታቶ
ከመቅደላ እስከ ላሊበላ
ከኢዞፕ እስከ ኢቶፕ
ከሐምሌት እስከ ኦቴሎ
ያ ፀጋዬ ማሎ ማሎ።
ከጩታ እስከ ፓሪስ
ከዊንጌት እስከ ምኒያፖሊስ
ልጅነቱን አነባብሮ
ዘበት እልፊቱን ተሻግሮ
ለብስለት ወዜማ ተቃጥሮ
ወለልቱው ስሎሞን ላይመተር ረዘመ
በዉርጭማ ሰማይ ላይጨበጥ ተመመ።
ይድረሰኝ ደብዳቤ ተርቢያለሁና"
ብሉ እንዳልማለደ
ንፋስን አማላጅ፣
ጨረቃን አዋላጅ፣
አርጎ እንዳልነጎደ
ገብሬ ኢልማ ደስታ እንደዘበት ሄደ
ኦክላሆማ ሜዳን ቤት አርጎት ለመደ።
ከዴህሊ እስከ ሎንዶን
ከይፋት እስከ ዋሽንግቶን
ባሻ አሸብር ባለ ቧልቱ
ደማሙ ብእረኛ አብዬ መንግስቱ
ያለ ፕሮብሌም አርፎ መተኛቱ!
ዮሐንስም ሄደ፣ ሰፊ አድማሱን አስታቅፎን
"እስኪ እናንተ ጎዱች ተጠየቁ" ብሎን
በብቸኝነት ነበልባል እንደነደደ
ቅኔው ይፋቴ ዳኛቸዉም ነጎደ
ኡኡታ አሮበት "እምቧ በሉ" እያለ
የጉራማይሌ ሕልሙን፣ ቁጭት እየፈተለ
ዮናስ በኩርምት ሞቱ እያሳለው ተከተለ
"እግዚያአብሔር ትመስን፣ ክብሯ ይስፋ" እንዳለ።
ደበበ በምናቡ ስይፍ ክትፎኛ ተካትፎ
ገሞራው በረከትን ሼጣንኛ ተራግሞ
የዜሮን ቁጥርነት ከአልፋው ሞግቶ
እውነት ለሚያንቀው አገጭ ይዞ ግቶ
ከዑራኤል ዳገት ሽቅብ እየቃኘን
"እኔም እንደናንተ ሕያው ነበርኩ" አለን።
አያ ሙሌም ምህላዉን ታክቶ
አጅሬው ከመንበሩ መኖሩን ሞግቶ
ክልትው አለ ብቻዉን፣ አዘመራውን እንደነዛ
በሱ የደም ጠብታ፣ የስንቱን ግንባር ሊያወዛ።
ከአባ ገዳ ኢልማ ገልማ
የማይድን በሽታ ነፍሱ አስታማ
ከመርካቶ እስከ ኮምፔሽታቶ
ከመቅደላ እስከ ላሊበላ
ከኢዞፕ እስከ ኢቶፕ
ከሐምሌት እስከ ኦቴሎ
ያ ፀጋዬ ማሎ ማሎ።
ከጩታ እስከ ፓሪስ
ከዊንጌት እስከ ምኒያፖሊስ
ልጅነቱን አነባብሮ
ዘበት እልፊቱን ተሻግሮ
ለብስለት ወዜማ ተቃጥሮ
ወለልቱው ስሎሞን ላይመተር ረዘመ
በዉርጭማ ሰማይ ላይጨበጥ ተመመ።
ዓርብ 1 ዲሴምበር 2017
ሀሴት-ወለድ ሙግት
ድንቅነትሽ እጡብ ድንቅ
ጨቅላ ፍጡር የሚያስቦርቅ
ነፀብራቅሽ ዘንጉ ረዥም
ከሰሜን ዋልታ አንስቶ፣
እስካንታርክቲካ የሚያንፀባርቅ
ያይኖችሽ ጦር ሰበቃ
ከሞት ታናሽ ወንድም፣
ብርሌ ነፍስ የሚያነቃ
ፈገግታሽ ላድማስ ቦግታው
የደመናትን መንጋ፣ ከሰማይ ላይ የሚመታው
ካለው፣ ካልነበረው
ከሌለው፣ ከሚኖረው
ተጣጥተን፣ ተፋልገን
ተራርበን፣ ተጣግበን
ዉል አልባ ተጣልፈን
አይፈቱት ተቋልፈን
ነግቶ እማኝ እንዳይሆን፣ አንሶላ ቀደድን
ክዋክብት ተጋፈን፣ በሸንጎ ቀለድን።
ጨቅላ ፍጡር የሚያስቦርቅ
ነፀብራቅሽ ዘንጉ ረዥም
ከሰሜን ዋልታ አንስቶ፣
እስካንታርክቲካ የሚያንፀባርቅ
ያይኖችሽ ጦር ሰበቃ
ከሞት ታናሽ ወንድም፣
ብርሌ ነፍስ የሚያነቃ
ፈገግታሽ ላድማስ ቦግታው
የደመናትን መንጋ፣ ከሰማይ ላይ የሚመታው
ካለው፣ ካልነበረው
ከሌለው፣ ከሚኖረው
ተጣጥተን፣ ተፋልገን
ተራርበን፣ ተጣግበን
ዉል አልባ ተጣልፈን
አይፈቱት ተቋልፈን
ነግቶ እማኝ እንዳይሆን፣ አንሶላ ቀደድን
ክዋክብት ተጋፈን፣ በሸንጎ ቀለድን።
ተጠየቅ እረኛ
ጠረቃሁ ለማታውቅ፣ ብትጠጣ ብትበላ
ለዚህች ለራስ ወዳድ፣ ላንዲት ከርስ ተድላ
ከገል ለተበጀች፣ ቁንፅል የዕድሜ ጀምበር
ዋስትና ለሌላት፣ ከሴኮንድ በኋላ እንደማትሰበር
ስንደዶ ቀንጥሰን፣ የገመድነው ጅራፍ
መልሶ ገረፈን፣ ባጦዝነው ሺህ እጥፍ።
ለዚህች ለራስ ወዳድ፣ ላንዲት ከርስ ተድላ
ከገል ለተበጀች፣ ቁንፅል የዕድሜ ጀምበር
ዋስትና ለሌላት፣ ከሴኮንድ በኋላ እንደማትሰበር
ስንደዶ ቀንጥሰን፣ የገመድነው ጅራፍ
መልሶ ገረፈን፣ ባጦዝነው ሺህ እጥፍ።
እኔን ሲዳኝ እኔ
አህያን ከጅብ ሳጣጥም
አይጥን ከድመት ሳሳስም
ዲስኩሬ በዉድ ሲያዋድድ
ፍም እሳትን ከደረቅ ጭድ
ልሣኔ ፈልጎ አቃርቦ
አራምባዉን ከቆቦ
ግና ምን አገኘኝ፣ ጎደልኩት ከራሴ
ደርሶ የሚከዳኝ፣ ጥሬ ቆይ ምላሴ።
አይጥን ከድመት ሳሳስም
ዲስኩሬ በዉድ ሲያዋድድ
ፍም እሳትን ከደረቅ ጭድ
ልሣኔ ፈልጎ አቃርቦ
አራምባዉን ከቆቦ
ግና ምን አገኘኝ፣ ጎደልኩት ከራሴ
ደርሶ የሚከዳኝ፣ ጥሬ ቆይ ምላሴ።
ሰኞ 30 ኦክቶበር 2017
አርዶ አደሮች ሆይ
ባሩድ እንደጠበል፣ በጅምላ እየረጩ
አረም ለማቆየት፣ ቡቃያ እየቀጩ
በደም ቀይ ምንጣፍ፣ ዛሬን ቢራመዱ
ነገ ሸንጎ 'ሚቀርብ፣ ዶሴ ነው መንገዱ።
አረም ለማቆየት፣ ቡቃያ እየቀጩ
በደም ቀይ ምንጣፍ፣ ዛሬን ቢራመዱ
ነገ ሸንጎ 'ሚቀርብ፣ ዶሴ ነው መንገዱ።
ቢሆንም ባይሆንም
የህልማለም ድግስ፣
ህላዌን አንጥሮ፣ ቢያጠጣም ቅቤ
አዋዝቶ ቢያጎርስም፣ ክትፎን ከአይቤ
ሰው ምኑ ሞኝ ነው፣
ገር ሕልሙን ተማምኖ፣ አይተኛ በራብ-ጥም
ጉምዥት ሳይጎነጭ፣ ተስፋ ሳይቆረጥም።
ህላዌን አንጥሮ፣ ቢያጠጣም ቅቤ
አዋዝቶ ቢያጎርስም፣ ክትፎን ከአይቤ
ሰው ምኑ ሞኝ ነው፣
ገር ሕልሙን ተማምኖ፣ አይተኛ በራብ-ጥም
ጉምዥት ሳይጎነጭ፣ ተስፋ ሳይቆረጥም።
እኔን ሲዳኝ እኔ
አህያን ከጅብ ሳጣጥም
አይጥን ከድመት ሳሳስም
ዲስኩሬ በዉድ ሲያዋድድ
ፍም እሳትን ከደረቅ ጭድ
ልሣኔ ፈልጎ አቃርቦ
አራምባዉን ከቆቦ
ግና ምን አገኘኝ፣ ጎደልኩት ከራሴ
ደርሶ የሚከዳኝ፣ ጥሬ ቆይ ምላሴ።
አይጥን ከድመት ሳሳስም
ዲስኩሬ በዉድ ሲያዋድድ
ፍም እሳትን ከደረቅ ጭድ
ልሣኔ ፈልጎ አቃርቦ
አራምባዉን ከቆቦ
ግና ምን አገኘኝ፣ ጎደልኩት ከራሴ
ደርሶ የሚከዳኝ፣ ጥሬ ቆይ ምላሴ።
ረቡዕ 25 ኦክቶበር 2017
በጫጉላ ጨረቃ
የናፍቆትን ጋራ፣ አሟምተሽ ስታልፊ
የትዝታን ግርዶሽ፣ ገላልጠሽ ስትገፊ
ድካምሽን ለማከም፣ በቀኝሽ ስታርፊ
የእንቅልፍ መንኩራኩር፣ ይዞሽ ሲመነጠቅ
የህልም ሰረገላ፣ አሳፍሮሽ ሲነጠቅ
ከማረፊያሽ ልቤ፣ ሰገነት ቁጭ እንዳልሽ
ያ'እዋፍ ሕብረ-ዜማ፣ ቀስቅሶ ካነቃሽ
ይልቅ ጆሮ ስጪ፣ ለማለዳው ዜማ
አዋጅ ይዟልና፣
በኔ የሚነገር፣ ባንቺ የሚሰማ።
የትዝታን ግርዶሽ፣ ገላልጠሽ ስትገፊ
ድካምሽን ለማከም፣ በቀኝሽ ስታርፊ
የእንቅልፍ መንኩራኩር፣ ይዞሽ ሲመነጠቅ
የህልም ሰረገላ፣ አሳፍሮሽ ሲነጠቅ
ከማረፊያሽ ልቤ፣ ሰገነት ቁጭ እንዳልሽ
ያ'እዋፍ ሕብረ-ዜማ፣ ቀስቅሶ ካነቃሽ
ይልቅ ጆሮ ስጪ፣ ለማለዳው ዜማ
አዋጅ ይዟልና፣
በኔ የሚነገር፣ ባንቺ የሚሰማ።
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
ልጥፎች (Atom)