ቃል ሲመነምን ሲቀጭጭ
አንደበት ሲነጥፍ ሲል ረጭ
አይገለጤን መግለጫ
ዝምታ ፍቱን ማምለጫ።
ሰኞ 14 ዲሴምበር 2015
እሑድ 8 ኖቬምበር 2015
ኑ
በጦርታችን ሰላም፣
በባርነታችን ነፃነት
በድቀታችን ጥንካሬ፣
በድንቁርናችን እውቀት
ኑ እንያያዝ እጅ ለእጅ
ኑ ተባብረን እንደርጅ ።
ሽንቁር እንስራ ደቅነን፣
ኑ ከሙሉ ባህር እንጥለቅ
የዋና ብስና እያገሳን፣
ኑ ከድቅድቅ ዝቅጠት እንዝለቅ።
ሆኖልን አያውቅምና፣
የፍቅርን አዝመራ ማጨድ
በነፋስ ሳቅ እንዲፈርሱ፣
ሞኝ ዱቄትና አመድ።
በባርነታችን ነፃነት
በድቀታችን ጥንካሬ፣
በድንቁርናችን እውቀት
ኑ እንያያዝ እጅ ለእጅ
ኑ ተባብረን እንደርጅ ።
ሽንቁር እንስራ ደቅነን፣
ኑ ከሙሉ ባህር እንጥለቅ
የዋና ብስና እያገሳን፣
ኑ ከድቅድቅ ዝቅጠት እንዝለቅ።
ሆኖልን አያውቅምና፣
የፍቅርን አዝመራ ማጨድ
በነፋስ ሳቅ እንዲፈርሱ፣
ሞኝ ዱቄትና አመድ።
ማን? መቼ?
ልብሽ ከልቤ እንዲዋሃድ
ደጅ ብጠና ስለመውደድ
ቀና ብለሽ ካንገትሽ
"እሱ ያለ 'ለት" ካልሽኝ
አመታት እንደዋዛ አለፉኝ።
ቆመው ሊቀሩ የነበሩ
አረፍ ሲሉ ከወንበሩ
አለሁ እንዳየሁ ወደ ላይ
"እሱ" ያልሽው ሳይገባኝ፣
እግዜርን ይሆን ወይ ሰማይ
አለሁ ሲመሽ ሲነጋ
ያንን እለት ፍለጋ።
ደጅ ብጠና ስለመውደድ
ቀና ብለሽ ካንገትሽ
"እሱ ያለ 'ለት" ካልሽኝ
አመታት እንደዋዛ አለፉኝ።
ቆመው ሊቀሩ የነበሩ
አረፍ ሲሉ ከወንበሩ
አለሁ እንዳየሁ ወደ ላይ
"እሱ" ያልሽው ሳይገባኝ፣
እግዜርን ይሆን ወይ ሰማይ
አለሁ ሲመሽ ሲነጋ
ያንን እለት ፍለጋ።
ማክሰኞ 3 ኖቬምበር 2015
ልንገርሽ'ማ
ያንቺ ብርቱ በሽታሽ
ያንቺ ክፉ ነቀርሳሽ ...
እንዳይመስልሽ ሆደ-ቅሪላ ጉበኛ
አይምሰልሽ ፍርድ ሚገመድል ዳኛ
እንዳይመስልሽ በሰፊ ምድርሽ ጠቦ አጥባቢ
አይምሰልሽ ታሪክ ደልዞ ቅራቅንቦ ከታቢ ...
ያንቺ ብርቱ በሽታሽ
ያንቺ ክፉ ነቀርሳሽ ...
እንዳይመስልሽ ድንበርሽን ጥሶ የመጣ
ከቶ አይምሰልሽ ያ ፀጉረ ለዋጣ ...
ያንቺ'ማ የጎን ዉጋትሽ!
ያንቺ'ማ የግር እሳትሽ!
ያንቺ'ማ ክፉ ደመኛሽ!
ያንቺ'ማ እኩይ ቀበኛሽ! ...
በአፍራሾችሽ ትብብር ፣ጠልቆ ሲቆፈር ጉድጓድሽ
አካፋ ዶማ ያቀበልኩ ፣ እኔው ራሴ ነኝ ጠላትሽ!
ያንቺ ክፉ ነቀርሳሽ ...
እንዳይመስልሽ ሆደ-ቅሪላ ጉበኛ
አይምሰልሽ ፍርድ ሚገመድል ዳኛ
እንዳይመስልሽ በሰፊ ምድርሽ ጠቦ አጥባቢ
አይምሰልሽ ታሪክ ደልዞ ቅራቅንቦ ከታቢ ...
ያንቺ ብርቱ በሽታሽ
ያንቺ ክፉ ነቀርሳሽ ...
እንዳይመስልሽ ድንበርሽን ጥሶ የመጣ
ከቶ አይምሰልሽ ያ ፀጉረ ለዋጣ ...
ያንቺ'ማ የጎን ዉጋትሽ!
ያንቺ'ማ የግር እሳትሽ!
ያንቺ'ማ ክፉ ደመኛሽ!
ያንቺ'ማ እኩይ ቀበኛሽ! ...
በአፍራሾችሽ ትብብር ፣ጠልቆ ሲቆፈር ጉድጓድሽ
አካፋ ዶማ ያቀበልኩ ፣ እኔው ራሴ ነኝ ጠላትሽ!
ሐሙስ 15 ኦክቶበር 2015
በምን ብልሃት
ከበራፍሽ ፈፋ
ፊትሽ ሳልደፋ
እንዳደይ አበባ
ሆ ብዬ ሳልገባ
እንደ ደራሹ ጎርፍ
ክንፌን ጥዬ ሳልከንፍ
እንደ ዲታ አፍቃሪ
ሳያሻኝ መስካሪ
መኖሬ ተጋርዶ ፣ በዚህ ሁሉ አማላይ
እንዴት ዉብ አይኖችሽ ፣ አረፉ ከእኔ ላይ።
ፊትሽ ሳልደፋ
እንዳደይ አበባ
ሆ ብዬ ሳልገባ
እንደ ደራሹ ጎርፍ
ክንፌን ጥዬ ሳልከንፍ
እንደ ዲታ አፍቃሪ
ሳያሻኝ መስካሪ
መኖሬ ተጋርዶ ፣ በዚህ ሁሉ አማላይ
እንዴት ዉብ አይኖችሽ ፣ አረፉ ከእኔ ላይ።
ቅዳሜ 5 ሴፕቴምበር 2015
በዘመን ባቡር ላይ
ለሰርክ ነጓጁ ፣ ብርቁ ላይደል ጉዞ
ክፉኛ ይከንፋል ፣ ባለጊዜ ብቻ በሆድ'ቃው ይዞ
ወደ አዲስ ዘመን ፣ተጓዥ እየጠራ
ሂያጁን ከሚቀረው ፣ ለቅሞ እያጠራ
የጊዜ ባቡሩ ፣ያልፋል እያጓራ።
ከውራ ፉርጎ ላይ ፣ እኔ አለሁ እንዳለሁ
ለጉድ የጎለተኝ ፣ ጭሱን እምጋለሁ
ጭሱን ገምሶ አልፎ ፣ ነፋስ ያወጋኛል
የዘመን ቱሩፋት ፣ ተስፋ ያበስረኛል
መጪው እኮ አደይ ነው ፣ እያለ ያፅናናኛል
ጨለማና ጭጋግ ፣ ሂያጅ ናቸው ይለኛል።
እኔ ደግሞ እላለሁ፣
"እብሪተኛን ሁላ ፣ በክንዴ እንዳልመከትሁ
ከአለትም አለት ፣ ሮሃን እንዳልነበርሁ
እንደ እፉዬ ጋላ ፣ ቀለለኝ ገላዬ
እንደሰማይ ኮከብ ፣ 'ራቀኝ ጥላዬ
እንደ ሙታን መንደር ፣ ጭራ'ለ ጓዳዬ
ከዘመን ገደል ዉስጥ ፣ወድቆ ገመናዬ።"
ቀጠለ ነፋሱ ጭስ እየገመሰ
ባቡሩም ገስግሶ ካንድ ዋሻ ደረሰ
ፍልፍል ያለት ዋሻ
ጣራው የነተበ በጭስ በጥቀርሻ
ከሩቅ ይጠራኛል ባማላይ ጥቅሻ
እንዲህ 'ሚል መስሎኛል፣
"ባታውቀው ነው እንጂ፣ ባታሰላስለው
ይህ ዋሻ አንተ ነህ፣ ጥቀርሻው ላብህ ነው
በዘመን ድማሚት ፣ በባለቀን መሮ
ወዘናና መቅኔህ ፣ ጅስሚህ ተቦርቡሮ
ይህ ዋሻ ታንፀ ፣ ካንተ ደምና'ጥንት
ባለጊዜ ብቻ ፣በፈጣኑ ባቡር ፣ እብስ እንዲልበት።
ካሮጌ ፍስሃው ፣ ወዳዲሱ ተድላው ፣ እንዲሻገርበት።"
ክፉኛ ይከንፋል ፣ ባለጊዜ ብቻ በሆድ'ቃው ይዞ
ወደ አዲስ ዘመን ፣ተጓዥ እየጠራ
ሂያጁን ከሚቀረው ፣ ለቅሞ እያጠራ
የጊዜ ባቡሩ ፣ያልፋል እያጓራ።
ከውራ ፉርጎ ላይ ፣ እኔ አለሁ እንዳለሁ
ለጉድ የጎለተኝ ፣ ጭሱን እምጋለሁ
ጭሱን ገምሶ አልፎ ፣ ነፋስ ያወጋኛል
የዘመን ቱሩፋት ፣ ተስፋ ያበስረኛል
መጪው እኮ አደይ ነው ፣ እያለ ያፅናናኛል
ጨለማና ጭጋግ ፣ ሂያጅ ናቸው ይለኛል።
እኔ ደግሞ እላለሁ፣
"እብሪተኛን ሁላ ፣ በክንዴ እንዳልመከትሁ
ከአለትም አለት ፣ ሮሃን እንዳልነበርሁ
እንደ እፉዬ ጋላ ፣ ቀለለኝ ገላዬ
እንደሰማይ ኮከብ ፣ 'ራቀኝ ጥላዬ
እንደ ሙታን መንደር ፣ ጭራ'ለ ጓዳዬ
ከዘመን ገደል ዉስጥ ፣ወድቆ ገመናዬ።"
ቀጠለ ነፋሱ ጭስ እየገመሰ
ባቡሩም ገስግሶ ካንድ ዋሻ ደረሰ
ፍልፍል ያለት ዋሻ
ጣራው የነተበ በጭስ በጥቀርሻ
ከሩቅ ይጠራኛል ባማላይ ጥቅሻ
እንዲህ 'ሚል መስሎኛል፣
"ባታውቀው ነው እንጂ፣ ባታሰላስለው
ይህ ዋሻ አንተ ነህ፣ ጥቀርሻው ላብህ ነው
በዘመን ድማሚት ፣ በባለቀን መሮ
ወዘናና መቅኔህ ፣ ጅስሚህ ተቦርቡሮ
ይህ ዋሻ ታንፀ ፣ ካንተ ደምና'ጥንት
ባለጊዜ ብቻ ፣በፈጣኑ ባቡር ፣ እብስ እንዲልበት።
ካሮጌ ፍስሃው ፣ ወዳዲሱ ተድላው ፣ እንዲሻገርበት።"
ማክሰኞ 18 ኦገስት 2015
አንዳንድ ቀን
እንዳንድ ቀን አለ፣
ምናብን እንዳክናፍ ፣ በሰፊ አዘርግቶ
ብረር ብረር ሚል ፣ ከምድር አስነስቶ።
ደሞ አለ አንዳንድ ቀን፣
ቢሆንን ሚያስመኝ ዘላለም አንድ ቀን
ጠራርጎ የሚሸኝ የ'ላዌን ሰቀቀን።
አንዳንድ ቀን አለ፣
ሳይጠሩት አቤት ባይ
ሳይልኩት ወዴት ባይ
ይሉትን አይሰማ ፣ ቃላባይ እንዳ'ባይ።
ደሞ አለ አንዳንድ ቀን፣
የቀን ባለቅኔ
በቆፈን ቆርብተህ ፣ ተቆራምተህ ሲያይህ
ሳጥን ሙሉ እርዛት፣ ደራርቦ ሚያለብስህ
ሌማት ሙሉ ጠኔ፣ ፈትፍቶ ሚያጎርስህ
እንጀትክን ሊያርስህ።
ምናብን እንዳክናፍ ፣ በሰፊ አዘርግቶ
ብረር ብረር ሚል ፣ ከምድር አስነስቶ።
ደሞ አለ አንዳንድ ቀን፣
ቢሆንን ሚያስመኝ ዘላለም አንድ ቀን
ጠራርጎ የሚሸኝ የ'ላዌን ሰቀቀን።
አንዳንድ ቀን አለ፣
ሳይጠሩት አቤት ባይ
ሳይልኩት ወዴት ባይ
ይሉትን አይሰማ ፣ ቃላባይ እንዳ'ባይ።
ደሞ አለ አንዳንድ ቀን፣
የቀን ባለቅኔ
በቆፈን ቆርብተህ ፣ ተቆራምተህ ሲያይህ
ሳጥን ሙሉ እርዛት፣ ደራርቦ ሚያለብስህ
ሌማት ሙሉ ጠኔ፣ ፈትፍቶ ሚያጎርስህ
እንጀትክን ሊያርስህ።
ረቡዕ 12 ኦገስት 2015
ሕይወት እንቆቅልሽ
ጠረኗ አይደገም ፣ ሁሌ አዲስ ላፍንጫ
ቀለሟ አይጨበጥ ፣ ነጭ ጥቁር ግራጫ
ሲለቋት እንክትክት ፣ ሲይዟት ሙልጭልጭ
ሲቀርቧት እርብትብት ፣ ሲርቋት ብልጭልጭ
ጀምበር ስትፈነጥቅ ፣ በፍካት ማለዳ
ሕይወት እንቆቅልሽ ፣ ሰርካ'ዲስ እንግዳ።
ቀለሟ አይጨበጥ ፣ ነጭ ጥቁር ግራጫ
ሲለቋት እንክትክት ፣ ሲይዟት ሙልጭልጭ
ሲቀርቧት እርብትብት ፣ ሲርቋት ብልጭልጭ
ጀምበር ስትፈነጥቅ ፣ በፍካት ማለዳ
ሕይወት እንቆቅልሽ ፣ ሰርካ'ዲስ እንግዳ።
ማክሰኞ 11 ኦገስት 2015
ተለመኑኝ
በብቸኝነት ቋቅታ ነው ፣ ከየልባችሁ መብቀሌ
በኗሪነታችሁ ትንሣኤ ነው ፣ ሞትን አንቄ መግደሌ
ከልቡናችሁ ኮትኩቱኝ ፣ እንዳልጠወልግ እንዳልደርቅ
ፍቅርን "እ..ፍ" በሉብኝ ፣ እንድለመልም እንድፀድቅ።
በኗሪነታችሁ ትንሣኤ ነው ፣ ሞትን አንቄ መግደሌ
ከልቡናችሁ ኮትኩቱኝ ፣ እንዳልጠወልግ እንዳልደርቅ
ፍቅርን "እ..ፍ" በሉብኝ ፣ እንድለመልም እንድፀድቅ።
ማክሰኞ 4 ኦገስት 2015
የልጅ ምኞት
ዋ...ልጅነት ችግኝነት
ለመፅደቅ ችኩልነት
በዘልማድ ምኞት ክንፈት
ንፁህ የሩቅ ሕልመኝነት
በድንገት ሀኪምነት (ድዌ ሊታከም)
በቅፅበት ማንዲስነት (ሊቃና ጥምም)
ቀና ብሎ አብራሪነት(ከንስር ሊቀደም)...
ዛሬ በብስለት ዋዜማ
የሕልሜን ድምፅ ስሰማ
ራሱን አድሷል ምኞቴ
ቢሳካልኝ ቢቀናኝ ፣ ብሆን ሲሶው ያ'ባቴ
ብታደለው ብመረጥ ፣ ብሆን ሩቧ የ'ናቴ
በሰውነቴ።
ለመፅደቅ ችኩልነት
በዘልማድ ምኞት ክንፈት
ንፁህ የሩቅ ሕልመኝነት
በድንገት ሀኪምነት (ድዌ ሊታከም)
በቅፅበት ማንዲስነት (ሊቃና ጥምም)
ቀና ብሎ አብራሪነት(ከንስር ሊቀደም)...
ዛሬ በብስለት ዋዜማ
የሕልሜን ድምፅ ስሰማ
ራሱን አድሷል ምኞቴ
ቢሳካልኝ ቢቀናኝ ፣ ብሆን ሲሶው ያ'ባቴ
ብታደለው ብመረጥ ፣ ብሆን ሩቧ የ'ናቴ
በሰውነቴ።
እሑድ 2 ኦገስት 2015
የተስያት ቆፈን
ከላይ የጠል ቁጣ
ከታች ምድር ቀልጣ
ላቤን ከጅማቴ ጠልቄ ቀዳለሁ
ከ'ሷ ጀርባ ቆሜ ተራ ጠብቃለሁ...
አርሳው ወይ ሸምታው ያልለየለት ጠጉሯ፣
መቃ አንገቷን ታ'ኮ
ችቦ'ገቧን አንቆ
ጉብታዉን ተንተርሶ
ሸለቆውን ባይኑ ልሶ
አደናቀፋት ስል ፣ አጋደማት ጠልፎ
ሽቅብ ይታዘባል ፣ ከቋንጃዋ አርፎ...
ሹክ ያልኳት ይመስል፣
ወደ ጎምዢው ፊቴ ፣ ፊቷን ብታዞረው
ቅፅበታዊ ቆፈን ፣ ጅስሚየን ወረረው...
ጉድ እኮ ነው!
ያጠመቀኝ ላቤ ወደ ላይ ተነነ?
የጠሃይዋ ቁጣ ከምኔው መነነ?
አሁን በዚህ ፍጥነት ፣ ተፈጥሮ ተዛባ?
ወይስ እዚሁ ቆሜ ፣ ክረምት ዘሎ ገባ?
ከታች ምድር ቀልጣ
ላቤን ከጅማቴ ጠልቄ ቀዳለሁ
ከ'ሷ ጀርባ ቆሜ ተራ ጠብቃለሁ...
አርሳው ወይ ሸምታው ያልለየለት ጠጉሯ፣
መቃ አንገቷን ታ'ኮ
ችቦ'ገቧን አንቆ
ጉብታዉን ተንተርሶ
ሸለቆውን ባይኑ ልሶ
አደናቀፋት ስል ፣ አጋደማት ጠልፎ
ሽቅብ ይታዘባል ፣ ከቋንጃዋ አርፎ...
ሹክ ያልኳት ይመስል፣
ወደ ጎምዢው ፊቴ ፣ ፊቷን ብታዞረው
ቅፅበታዊ ቆፈን ፣ ጅስሚየን ወረረው...
ጉድ እኮ ነው!
ያጠመቀኝ ላቤ ወደ ላይ ተነነ?
የጠሃይዋ ቁጣ ከምኔው መነነ?
አሁን በዚህ ፍጥነት ፣ ተፈጥሮ ተዛባ?
ወይስ እዚሁ ቆሜ ፣ ክረምት ዘሎ ገባ?
ከአዕላፍ በስቲያ
ከልክነት ልኬት ልቆ
ከመሳሳት ስቀት ርቆ
ትናንትና ከሽልቡ ነቅቶ
ዛሬ ባንኖ ተንጠራርቶ
ነገ ቀድሞ ካልተኛበት
የቀን ውድቅት ካልሆነበት
ፍቅር ጥንቡን ካልጣለበት
ቆሜያለሁኝ ከፊት ጀርባ
ከኔና አንቺ የሐቅ አምባ።
ከመሳሳት ስቀት ርቆ
ትናንትና ከሽልቡ ነቅቶ
ዛሬ ባንኖ ተንጠራርቶ
ነገ ቀድሞ ካልተኛበት
የቀን ውድቅት ካልሆነበት
ፍቅር ጥንቡን ካልጣለበት
ቆሜያለሁኝ ከፊት ጀርባ
ከኔና አንቺ የሐቅ አምባ።
ሐሙስ 23 ጁላይ 2015
የዛሬን አያርገውና
በማንነት ሐርግ ተጠልፈን፣ ባፍጢማችን ሳንደፋ
ባይማኖት ሰይፍ ተካትፈን ፣ ደምራቃችንን ሳንተፋ
በፖለቲካ ጎራ ተቧድነን ፣ በርዕዮታለም ሳንወድቅ
በሀብት መደብ ተከፍለን ፣ በንዋይ ክንድ ሳንደቅ
በፍቅር ክር የተሳሰርን
በሰብአዊነት የተጋመድን
የዛሬን አያርገውና ፣ ሁላችንም ሰዎች ነበርን።
ባይማኖት ሰይፍ ተካትፈን ፣ ደምራቃችንን ሳንተፋ
በፖለቲካ ጎራ ተቧድነን ፣ በርዕዮታለም ሳንወድቅ
በሀብት መደብ ተከፍለን ፣ በንዋይ ክንድ ሳንደቅ
በፍቅር ክር የተሳሰርን
በሰብአዊነት የተጋመድን
የዛሬን አያርገውና ፣ ሁላችንም ሰዎች ነበርን።
ረቡዕ 15 ጁላይ 2015
ይታወሱ
ጥሬ እኔን ሲያሞክኩ ፣ ከስለው በዚያው የቀሩ
ብሌናቸዉን ያሟሙ ፣ የኔን አይኖች ሲያበሩ
ቃራሚ ጆሮዬን ሲስሉ ፣ መስሚያቸው የዶለዶመ
ድዌዬን ዞትር ሲያክሙ ፣ ኩለንተናቸው የታመመ
እነማን እንደነበሩ፣
እስቲ ይታወሱ እነርሱ
እስቲ ይታወሱ በስሱ።
በደማቸው እንድወፍር ፣ ሞጌያቸው ፈጦ የወጣ
ወዛቸው አመዴን ሲያብስ ፣ ገጥታቸው የገረጣ
የደም ገንቦየን ሲሞሉ፣ የደም ሥራቸው የነቃ
ዋስ ምስክር ላጥቱ ፣ ለኔ እንዳልቆሙ ጠበቃ
እነማን እንደነበሩ፣
እስቲ ይታወሱ እነርሱ
እስቲ ይታወሱ በስሱ።
ባለጌ አንገቴን ሲያቀኑ ፣ ጭምት አንገታቸው የተደፋ
ሳንቃ ደረታቸውን የሰጡ ፣ ሸምበቆ ደረቴን እንድነፋ
የፍዳ ባህር ሳቋርጥ ፣ ሰርጓጅ መርከቤ የነበሩ
የመከራን ወንዝ ስሻገር ፣ ተጋድመው ድልድዬን የሠሩ
ደስታና ኡምራቸውን ፣ በአንድነት ለኔ የገበሩ
እነማን እንደነበሩ
እስቲ ይታወሱ እነርሱ
እስቲ ይታወሱ በስሱ።
ዓርብ 19 ጁን 2015
ላንድ የዋህ ፈረንጅ
<<እየደጋገመ ጠኔ ሚጥላቸው
ያንተ ሀገር ሰዎች ረሃብተኞች ናቸው>>
ላልከኝ የዋህ ፈረንጅ
መልስ አለኝ የሚፋጅ...
ምንም ባዶ ቢሆን ፣ አንጀት ማጀታቸው
የኔ ሀገር ሰዎች ፣ ርቅቅ ያሉ ናቸው
ጦማቸዉን አያድሩም ፣ ጦማቸውን አንደዋሉ
ጎናቸው አርፎ አያውቅም ፣ አንድ ነገር ካልበሉ።
ያንተ ሀገር ሰዎች ረሃብተኞች ናቸው>>
ላልከኝ የዋህ ፈረንጅ
መልስ አለኝ የሚፋጅ...
ምንም ባዶ ቢሆን ፣ አንጀት ማጀታቸው
የኔ ሀገር ሰዎች ፣ ርቅቅ ያሉ ናቸው
ጦማቸዉን አያድሩም ፣ ጦማቸውን አንደዋሉ
ጎናቸው አርፎ አያውቅም ፣ አንድ ነገር ካልበሉ።
ሐሙስ 18 ጁን 2015
ዞትር ሕያውነት
በትቢያነቱ ጊዜ፣
ከፍግ ተዳብሎ ተጣለ
ለምለም ሣር ሆኖ ከች አለ!
በሣርነቱ ዘመን፣
በጥርስ መንጋ ተጋጠ
ተመንዥጎ ተሰለቀጠ
ከድቀቱ ዉርጅብኝ ፣ በሬ ሆኖ አመለጠ!
በበሬነቱ ጊዜ፣
አፈር ሲገፋ ሰነበተ
ባንዲት የቁርጥ ቀን። ታርዶ ተበለተ
አፅሙን በሥጋ ሸፍኖ ፣ ሰው ሆኖ ተከሰተ!
እሱ እቴ፣
ሰርክ ኗሪነቱ እየደረጀ
ላዲስ ህይወቱ ጥርጊያ መንገድ እያበጀ
ዞትር ይመጣል ሄደ ሲሉት
በገደብ አልባ ሕያውነት።
ከፍግ ተዳብሎ ተጣለ
ለምለም ሣር ሆኖ ከች አለ!
በሣርነቱ ዘመን፣
በጥርስ መንጋ ተጋጠ
ተመንዥጎ ተሰለቀጠ
ከድቀቱ ዉርጅብኝ ፣ በሬ ሆኖ አመለጠ!
በበሬነቱ ጊዜ፣
አፈር ሲገፋ ሰነበተ
ባንዲት የቁርጥ ቀን። ታርዶ ተበለተ
አፅሙን በሥጋ ሸፍኖ ፣ ሰው ሆኖ ተከሰተ!
እሱ እቴ፣
ሰርክ ኗሪነቱ እየደረጀ
ላዲስ ህይወቱ ጥርጊያ መንገድ እያበጀ
ዞትር ይመጣል ሄደ ሲሉት
በገደብ አልባ ሕያውነት።
እሑድ 14 ጁን 2015
እሑድ 24 ሜይ 2015
ሀገሬ
ቅኔ ናት ሀገሬ ፣ ባለ ሰምና ወርቅ
አስለቃሿን ስታይ ፣ ከ'ት ብላ ምትስቅ።
ሀገሬ ቅኔ ናት ፣ ባለ ሰምና ወርቅ
ሚያከስላትን እቶን ፣ ለቆፈኗ ምትሞቅ።
ቅኔ ናት ሀገሬ ፣ ባለ ወርቅና ሰም
ባላንጣዋን አቅፋ ፣ አጥብቃ ምትስም።
አስለቃሿን ስታይ ፣ ከ'ት ብላ ምትስቅ።
ሀገሬ ቅኔ ናት ፣ ባለ ሰምና ወርቅ
ሚያከስላትን እቶን ፣ ለቆፈኗ ምትሞቅ።
ቅኔ ናት ሀገሬ ፣ ባለ ወርቅና ሰም
ባላንጣዋን አቅፋ ፣ አጥብቃ ምትስም።
የእናት እንጉርጉሮ
ባዶ አንጀቱ እንደቆሰለ
ፊቱ በንዳድ እንደከሰለ
ቆራጥ ሃሞቱን እንደቋጠረ
ልጄ እንደወጣ በቀረ...
ያዘን ጎርፍ ገፍቶኝ ፣ ቢጥለኝ ፊታቸው
ተሽቀርቅረው መጡ ፣ በዋና ልብሳቸው
የ'ንባዬ ቦይ ስፋት ፣ ዉቅያኖስ መስሏቸው።
ልጄስ ወድቆ ቀረ ፣ ላንዴ እስከ ወዲያኛው
ምሬቴን ማርከሻ ፣ ምን ይሆን መፅናኛው?
ለፍርድ መማፀኛ ፣ በተዘረጋ እጄ
እዝን አስጨበጡኝ ፣ ጅብ ለበላው ልጄ።
-----------------------------------------
(ከተኩላ ሲሸሹ በጅብ ለተበሉት)
ፊቱ በንዳድ እንደከሰለ
ቆራጥ ሃሞቱን እንደቋጠረ
ልጄ እንደወጣ በቀረ...
ያዘን ጎርፍ ገፍቶኝ ፣ ቢጥለኝ ፊታቸው
ተሽቀርቅረው መጡ ፣ በዋና ልብሳቸው
የ'ንባዬ ቦይ ስፋት ፣ ዉቅያኖስ መስሏቸው።
ልጄስ ወድቆ ቀረ ፣ ላንዴ እስከ ወዲያኛው
ምሬቴን ማርከሻ ፣ ምን ይሆን መፅናኛው?
ለፍርድ መማፀኛ ፣ በተዘረጋ እጄ
እዝን አስጨበጡኝ ፣ ጅብ ለበላው ልጄ።
-----------------------------------------
(ከተኩላ ሲሸሹ በጅብ ለተበሉት)
ሰኞ 16 ማርች 2015
እሑድ 1 ማርች 2015
የዜግነት ነገር
እኔስ ብዬ ነበር፣
ዓለም ናት ሃገሬ
የሰው ዘር ነው ዘሬ
ወንዛ ወንዙ ወንዜ ፣ ሰፈሩ ሰፈሬ።
እኔስ ብዬ ነበር፣
ስፍሩ ነው ስፍሬ
ቁጥሩ ነው ቁጥሬ።
እኔስ ብዬ ነበር፣
አርቆ ላጤነው ፣ ከቅዥት ባሻገር
ሕልሜ ድንበር-የለሽ ፣ አድማስ'ሚሻገር።
እኔስ ብዬ ነበር ፣ ሰው ሁሉ ያገሬ ልጅ
ማጀቱ ማጀቴ ፣ ደጃፉ ለኔም ደጅ።
ካለም ተነጥዬ ፣ ካገር እንድረጋ
ሳልወድ ለጠፉብኝ ፣ ፓስፖርት ይሉት ታርጋ
ብጎመዥ ብቋምጥ ፣ ላልሆን ያለም ዜጋ።
ዓለም ናት ሃገሬ
የሰው ዘር ነው ዘሬ
ወንዛ ወንዙ ወንዜ ፣ ሰፈሩ ሰፈሬ።
እኔስ ብዬ ነበር፣
ስፍሩ ነው ስፍሬ
ቁጥሩ ነው ቁጥሬ።
እኔስ ብዬ ነበር፣
አርቆ ላጤነው ፣ ከቅዥት ባሻገር
ሕልሜ ድንበር-የለሽ ፣ አድማስ'ሚሻገር።
እኔስ ብዬ ነበር ፣ ሰው ሁሉ ያገሬ ልጅ
ማጀቱ ማጀቴ ፣ ደጃፉ ለኔም ደጅ።
ካለም ተነጥዬ ፣ ካገር እንድረጋ
ሳልወድ ለጠፉብኝ ፣ ፓስፖርት ይሉት ታርጋ
ብጎመዥ ብቋምጥ ፣ ላልሆን ያለም ዜጋ።
ረቡዕ 18 ፌብሩዋሪ 2015
ጭጋጎ
ክረምት ይሉት ወፍራም ምፀት
ይህን ብርድ ብሎ ማለት ዘበት
ዛፉ አርቃኑን ፈትሎ ለብሶ
ሳሩ በነጭ ጭቃ ተለውሶ
አፌ የዉርጭ ነበልባል አየተፋ
እግሬ ሰማይ ያቦካውን ሊጥ አየገፋ...
ይህን ብርድ ብሎ ማለት ዘበት
ዛፉ አርቃኑን ፈትሎ ለብሶ
ሳሩ በነጭ ጭቃ ተለውሶ
አፌ የዉርጭ ነበልባል አየተፋ
እግሬ ሰማይ ያቦካውን ሊጥ አየገፋ...
በርዳ'ማትበርደው ነፍሴ
ላፍታ አፈትልካ ከዉርጩ ናዳ
በዱቄት ዳመና ሰርጋ ነጉዳ
ያገሬን ለጋስ ጠሃይ ሞቃ ሞቃ
ሳታገግም ፣ ሳትጠረቃ
በቆፈን ላብ ተጠምቄ ፣ ከቁም ድንዛዜ ስነቃ...
አገኘሁት በድን ገላዬን ፣ ከጭጋጋማው ከተማ
ዋቲው ማቲው ተከናንቦ ፣ አጫ በረዶ ሸማ።
ላፍታ አፈትልካ ከዉርጩ ናዳ
በዱቄት ዳመና ሰርጋ ነጉዳ
ያገሬን ለጋስ ጠሃይ ሞቃ ሞቃ
ሳታገግም ፣ ሳትጠረቃ
በቆፈን ላብ ተጠምቄ ፣ ከቁም ድንዛዜ ስነቃ...
አገኘሁት በድን ገላዬን ፣ ከጭጋጋማው ከተማ
ዋቲው ማቲው ተከናንቦ ፣ አጫ በረዶ ሸማ።
ሰኞ 26 ጃንዋሪ 2015
ከሁለት አጣሁ
እኔ ችግኝ ሆኘ ፣ አንች አትክልተኛ
መኮትኮቻሽ ዱልዱም ፣ ማረሚያሽ መናኛ
ለይቶልኝ አልጠወለግሁ
አድሎኝም አልለመለምሁ
ዳግም ላልጠረቃ ቀነጨርሁ።
መኮትኮቻሽ ዱልዱም ፣ ማረሚያሽ መናኛ
ለይቶልኝ አልጠወለግሁ
አድሎኝም አልለመለምሁ
ዳግም ላልጠረቃ ቀነጨርሁ።
ማክሰኞ 13 ጃንዋሪ 2015
እሪ በከንቱ
ከመሃል ፒያሳ ፣ ወደ እሪ-በከንቱ ፣ በሚወስደን መንገድ
እንደዋዛ አየናት ፣ ጠሐይ ያላመሏ ፣ በእሳት ስትማገድ
ምን ይልክ አፅሟ ፣ ምን ይልክ አጥንቷ
የ'ቴጌ ጣይቱ ፣ የልበ-ብርሃኒቷ
የትውልዴ ዜማ ፣ ድርድሩና ምቱ
እሪ ነው ፣ እሪ ነው ፣ እሪ ነው በከንቱ!
እንደዋዛ አየናት ፣ ጠሐይ ያላመሏ ፣ በእሳት ስትማገድ
ምን ይልክ አፅሟ ፣ ምን ይልክ አጥንቷ
የ'ቴጌ ጣይቱ ፣ የልበ-ብርሃኒቷ
የትውልዴ ዜማ ፣ ድርድሩና ምቱ
እሪ ነው ፣ እሪ ነው ፣ እሪ ነው በከንቱ!
ዓርብ 9 ጃንዋሪ 2015
ለምን ተሰደደ?
"ለምን ተሰደደ?" ፣ ለሚል ልብ አውላቂ
ጆሮዉ ለቆመበት ፣ መልስ-አወቅ ጠያቂ
ብላችሁ ንገሩት!
ለእልፍ አልፎ-ሂያጆች ፣ ጥላና ከለላ በነበረች ሀገር
በብዙሃኑ ላብ ጥቂቶች ሲኖሩ ታከተው ማኗኗር።
በመወለድ ቋንቋ ፣ በዜግነት ልኬት ፣ ምን ቢሆን አንደኛ
ቀና ባለ ቁጥር አንገት እያስደፉት ፣ በተዋረድ ወርዶ ፣ ቢሆን ሰባተኛ።
የመገፋት ጋራ ፣ መግፋት አንገሽግሾት
የበይ ተመልካች ፣ መሆን አቅለሽልሾት
ብላችሁ ንገሩት!
የሞተላት ሳይሆን ፣ ገዳይዋ ሊበላ
ሃገሩን በቅርጫ መበለት-መካፈል ፣ ባይሆንለት መላ።
ከችጋር ችንካሩ ፣ ተላቆ ሊራመድ
ስንዝር መሬት ቢያጣ ፣ በሮቹን ለመጥመድ።
የተከሰከሰው ያባቶቹ አጥንት ፣ አጥንቱን ቆርቁሮት
በትንባሆ ዋጋ ቀዬው ሲቸረቸር ፣ ቆሽቱን አሳርሮት።
ብላችሁ ንገሩት!
** ** ** ** ** **
"ለምን ተሰደደ?" ፣ ለሚል ልብ አውላቂ
ጆሮዉ ለቆመበት ፣ መልስ-አወቅ ጠያቂ
አሁንም ንገሩት!
በኡኡታው ፣ ቢመነጠር
በዝምታው ፣ ቢጠረጠር
ከመሃል ዳር ቢወረወር።
ብላችሁ ንገሩት!
በአብሮነት ጥማት ፣ በሃሩር ቢንቃቃ
በአድምጡኝ ተማፅኖ ፣ ጎሮሮው ቢነቃ
በልዩነት ደወል ፣ ከንቅልፉ ቢነቃ።
የነፃነት አሊፍ፣
የ'ኩልነት ሆሄ፣
የፍትህ ፣ የርትእ ፣ የፍርድ አቡጊዳ
ያልገባው ነፃ'ውጪ ፣ አንድ-ሁለት አስብሎ ቢያስቆጥረው ፍዳ
ብላችሁ ንገሩት!
** ** ** ** ** **
"ጨርቁን ማቁን ሳይል ካገር የበነነ
ምነው ወንድም-ዓለም እንዲህ የጨከነ?"
ብሎ ለሚጠይቅ መልስ-አወቅ ጠያቂ
ብላችሁ ንገሩት!
ስጋዋ ተግጦ ፣ ደሟ ተመጥምጦ
አጥንቷ ተሰብሮ ፣ መቅኔዋ ተመጦ
የሀገሩን ቅሪት ፣ ቢያይ ልቡ ደምቶ
እሷን ሚያወሳው ፣ ምናምኒት ጠልቶ
ነፍሴ አውጭኝ ብሏል ፣ ከቀን ጅቦች ሸሽቶ።
ብላችሁ ንገሩት!
"ለምን ተሰደደ?" ፣ ለሚል ልብ አውላቂ
ጆሮዉ ለቆመበት ፣ መልስ-አወቅ ጠያቂ።
ጆሮዉ ለቆመበት ፣ መልስ-አወቅ ጠያቂ
ብላችሁ ንገሩት!
ለእልፍ አልፎ-ሂያጆች ፣ ጥላና ከለላ በነበረች ሀገር
በብዙሃኑ ላብ ጥቂቶች ሲኖሩ ታከተው ማኗኗር።
በመወለድ ቋንቋ ፣ በዜግነት ልኬት ፣ ምን ቢሆን አንደኛ
ቀና ባለ ቁጥር አንገት እያስደፉት ፣ በተዋረድ ወርዶ ፣ ቢሆን ሰባተኛ።
የመገፋት ጋራ ፣ መግፋት አንገሽግሾት
የበይ ተመልካች ፣ መሆን አቅለሽልሾት
ብላችሁ ንገሩት!
የሞተላት ሳይሆን ፣ ገዳይዋ ሊበላ
ሃገሩን በቅርጫ መበለት-መካፈል ፣ ባይሆንለት መላ።
ከችጋር ችንካሩ ፣ ተላቆ ሊራመድ
ስንዝር መሬት ቢያጣ ፣ በሮቹን ለመጥመድ።
የተከሰከሰው ያባቶቹ አጥንት ፣ አጥንቱን ቆርቁሮት
በትንባሆ ዋጋ ቀዬው ሲቸረቸር ፣ ቆሽቱን አሳርሮት።
ብላችሁ ንገሩት!
** ** ** ** ** **
"ለምን ተሰደደ?" ፣ ለሚል ልብ አውላቂ
ጆሮዉ ለቆመበት ፣ መልስ-አወቅ ጠያቂ
አሁንም ንገሩት!
በኡኡታው ፣ ቢመነጠር
በዝምታው ፣ ቢጠረጠር
ከመሃል ዳር ቢወረወር።
ብላችሁ ንገሩት!
በአብሮነት ጥማት ፣ በሃሩር ቢንቃቃ
በአድምጡኝ ተማፅኖ ፣ ጎሮሮው ቢነቃ
በልዩነት ደወል ፣ ከንቅልፉ ቢነቃ።
የነፃነት አሊፍ፣
የ'ኩልነት ሆሄ፣
የፍትህ ፣ የርትእ ፣ የፍርድ አቡጊዳ
ያልገባው ነፃ'ውጪ ፣ አንድ-ሁለት አስብሎ ቢያስቆጥረው ፍዳ
ብላችሁ ንገሩት!
** ** ** ** ** **
"ጨርቁን ማቁን ሳይል ካገር የበነነ
ምነው ወንድም-ዓለም እንዲህ የጨከነ?"
ብሎ ለሚጠይቅ መልስ-አወቅ ጠያቂ
ብላችሁ ንገሩት!
ስጋዋ ተግጦ ፣ ደሟ ተመጥምጦ
አጥንቷ ተሰብሮ ፣ መቅኔዋ ተመጦ
የሀገሩን ቅሪት ፣ ቢያይ ልቡ ደምቶ
እሷን ሚያወሳው ፣ ምናምኒት ጠልቶ
ነፍሴ አውጭኝ ብሏል ፣ ከቀን ጅቦች ሸሽቶ።
ብላችሁ ንገሩት!
"ለምን ተሰደደ?" ፣ ለሚል ልብ አውላቂ
ጆሮዉ ለቆመበት ፣ መልስ-አወቅ ጠያቂ።
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
ልጥፎች (Atom)