ሰኞ 16 ዲሴምበር 2013

ያለሰበብ የምወድሽ

ፍቅሬ ለኔ ምኔ?
ዘወትር ጠይቂያለሁ
በርካሽ መለኪያ ፣
ሁሌም መትሪያለሁ

ደም ግባት ቁመና ፣
ዳሌና ወዘና

በረዶ ጥርሶቿ ፣
ጨረቃ አይኖቿ

ጣቶቿ አለንጋ ፣
አፍንጫ ሰልካካ

ያ መቃው አንገቷ ፣
ያ ሳንቃው ደረቷ

ጀምሬ ከራስ ፀጉሯ ፣
ፈፅሜ በእግር ጥፍሯ

የሰውነት አካል ፣
ሳስቀምጥ ሳነሳ
ሳደንቅሽ ስክብሽ ፣
ጥያቄው ተረሳ።

በጥልቀት ሳስበው ፣
ያንቺን ትርጉም ለኔ
እጅግ ያንስብኛል ፣
ማለት ግማሽ ጎኔ

አካልሽ ቢያምርም ፣
ብዙም አልመሰጠኝ
አይንህ ላፈር ብለሽ ፣
ብትፈልጊ ሸኚኝ
አፈር ስገባልሽ ፣
ብቻ አንዴ ስሚኝ...

ያለሰበብ ያለምክንያት ፣
በሞኝነት የምወድሽ
አካልሽን ሸፍኖት ነው ፣
የማረከኝ ሰው-ነትሽ ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ