የብርሃኑ ስንኞች
የስነ-ግጥም ጦማር
Home
About
ማክሰኞ 3 ዲሴምበር 2013
በራስ መድመቅ
ካነበብከው አንድ መፅሐፍ ፣ እንቶ ፈንቶ እያቀለምክ
አገሬዉን አታደንቁር ፣ አዲስ ግኝት አንዳበሰርክ
ከህሊናህ ባህር ቀድተህ ፣ ያቀረብከው አዲስ ሃሳብ
ሳትኩለው ሳትቀባው ፣ ማብራቱ አይቀር እንደ ኮከብ
የሰው ወርቅ ተደግፈህ ፣ ባጉል ኩራት ከምትቀልጥ
የራስህን መዳብ ይዘህ ፣ ብትወድቅ እንኳ ተንፈራገጥ ::
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ
በጣም አዲስ ልጥፍ
የቆየ ልጥፍ
መነሻ
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
አስተያየቶች ለጥፍ (Atom)
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ