አሳልፈን ሰጥተን ፣ መስሎን የሚመለስ
የማሰብ ነፃነት ፣ እስኪቀረን ድረስ
አንኳንስ በአካል ፣ አይታይ በመንፈስ።
አኛ ያቀድነዉን ፣ ሌላ እንዲሰራልን
ተቀምጠን ስንጠብቅ ፣ ነፃ የሚያወጣን
አዚህ ክፍት እስር ቤት ፣ አረጀን ሻገትን።
ከፍርሃት እንቅልፍ ፣ በርግገን ከነቃን
እኔ ማለት ቀርቶ ፣ ለኛ ዘብ ከቆምን
ጎጠኝነት ሳይሆን ፣ ሰው መሆን ካስማማን
ከዛሬ አሻግረን ፣ ነገን ከተለምን
ለነፃነታችን ፣ እጅጉን ቅርብ ነን።
ተምረን ከሆነ፣ ካምናና ካቻምና
እርምጃችን ይሁን ፣ ሁሌም በጥሞና
ነፃነት በነፃ ፣ አይገኝምና።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ