ሐሙስ 19 ዲሴምበር 2013

ሆድና ህሊና

የዛሬ ስንት ዓመት ፣ በነፃነት ማግስት
ህሊና ገጠመ ፣ ከሆዱ ጋር ሙግት
ከየጎራው ወጡ ፣ የፍትህ አማልክት።

ያልታወረ ህሊና ፣ ብሩህ ያገር ተስፋ
ሊቀጥል አላሻም ፣ወትሮ እንደተከፋ።

የሰላምን እሳት ፣ ላንቃዎች ለኮሱ
ብዕሮችም አልቀሩ ፣ እንደመነኮሱ።

የማይዝሉ አጆች ፣ የማይደክም አንደበት
ማን ሊመልሳቸው ፣ አብረው ባንድነት።

ህሊና ተርቦ ፣ ሆድ ከሚቀፈደድ
ባድር ባዮች ሴራ ፣ ሁሌ ከመሳደድ
ሳይሻል አይቀርም ፣ ጨርቅ ጥሎ ማበድ።

እብድስ ከለየለት ፣ ማንም ያዝንለታል
ጨርቁን እንኳን ቢጥል ፣ ዉራጅ ያለብሱታል
የሚበላው ቢያጣ ፣ ሰይጣን ያጎርሰዋል
አዉቆ አበድ መሆን ነው ፣ ከሁሉ 'ሚያስጠላ
እርባና የሌለው ፣ የሰው ቀጥፎ-በላ።

እብዶችም አይደሉ ፣ ወይ አውቆ አበዶች
ወገንም አይደሉ ፣ ወይ ጠላት መሳዮች
ከዚህ እየወሰዱ ፣ ከዚያ አቀባዮች
ከዚህ እየነቀሉ ፣ ከወዲያ ተካዮች
ከዚህ እያቦኩ ፣ ከዚያ ጋጋሪዎች
እዉነት ትፍረዳቸው ፣ እኚህን ጡት ነካሾች ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ