የብርሃኑ ስንኞች
የስነ-ግጥም ጦማር
Home
About
ረቡዕ 12 ማርች 2014
ወሊድ-አልባ ምጥ
መክኗል እንዳይባል ፣
የብሶት ምርጥ ዘር ፣ የኋሊት አዳቅሎ
በሕሊናው ማህፀን፣ ይዟል አንጠልጥሎ።
ጨንግፏል እንዳንል፣
ሌት ተቀን በማማጥ ፣ ሲቀመጥ ሲነሳ
ጭቆና ያጎበጠው ፣ አንድ ወገቡ ሳሳ።
አዋላጁም ሆኖ ፣ የሌለው እርባና
ምጡም ወሊድ-አልባ ፣ አስጨናቂ ሆነና
ሽሉን ተሸክመን ፣ ነግቶ እየጠባ
የሚወለደውን ፣ ስንጠብቅ ባበባ
አፈር ላይ ያለነው አፈር እንዳንገባ።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ
በጣም አዲስ ልጥፍ
የቆየ ልጥፍ
መነሻ
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
አስተያየቶች ለጥፍ (Atom)
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ