የብርሃኑ ስንኞች
የስነ-ግጥም ጦማር
Home
About
ረቡዕ 12 ማርች 2014
ያላወቅከው
እንደንጋት ጮራ፣
ከሚያበራው ፈገግታዬ
እንደበረዶ ነጥቶ፣
ከሚያስካካው ጥርሴ
እቅፍ ሳም አርገኝ፣
ከሚለው ገላዬ
.
.
.
ከዚህ ሁሉ ጀርባ መሽጎ
አንተን 'ሚታዘብህ ተሸሽጎ
የዋህነትህን 'ሚያይ አጮልቆ
እድሜ ዘመንህን ብትሰጠው
ተመራምረህ 'ማትጨብጠው
በልቤ ጓዳ የቋጠርኩት
አለ ያልገባህ ጠጣር እውነት
ስውር የታሪክ ጉንጉን ስፌት።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ
በጣም አዲስ ልጥፍ
የቆየ ልጥፍ
መነሻ
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
አስተያየቶች ለጥፍ (Atom)
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ