ቅዳሜ 8 ማርች 2014

ዉሻና ሰው

ሰውና ዉሻማ ፣ ምን አንድ አድርጓቸው
ለሰው የማይዋጥ ፣ ልዩነት አላቸው።
የተራበ ዉሻ ፣ የጠገበ ለታ
ተመልሶ አይነክስም ፣ ያበላዉን ጌታ
የተራበ ሰው ግን ፣
የቀረበለትን ፣ አንድ ሁለቴ ጎርሶ
ደረቅ ጎሮሮውን ፣ በምፅዋት አርሶ
ጠኔ ያደከማት ፣ ነፍሱ መለስ ስትል
ይጎነጉነዋል ፣ የተንኮሉን ፈትል።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ