የብርሃኑ ስንኞች
የስነ-ግጥም ጦማር
Home
About
ቅዳሜ 8 ማርች 2014
ዉሻና ሰው
ሰውና ዉሻማ ፣ ምን አንድ አድርጓቸው
ለሰው የማይዋጥ ፣ ልዩነት አላቸው።
የተራበ ዉሻ ፣ የጠገበ ለታ
ተመልሶ አይነክስም ፣ ያበላዉን ጌታ
የተራበ ሰው ግን ፣
የቀረበለትን ፣ አንድ ሁለቴ ጎርሶ
ደረቅ ጎሮሮውን ፣ በምፅዋት አርሶ
ጠኔ ያደከማት ፣ ነፍሱ መለስ ስትል
ይጎነጉነዋል ፣ የተንኮሉን ፈትል።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ
በጣም አዲስ ልጥፍ
የቆየ ልጥፍ
መነሻ
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
አስተያየቶች ለጥፍ (Atom)
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ