የብርሃኑ ስንኞች
የስነ-ግጥም ጦማር
Home
About
እሑድ 30 ማርች 2014
ተበልታ
ተደግፋ ባጥንት
ተመርጋ በሥጋ
ተለስና በደም፣
እንቡጦቿን ቀጥፋ
ክፉ ዘመን አልፋ
ደብዛዋ ቢጠፋ፣
በየአደባባዩ ስፈልግ ስማስን
በደግ ሲነሳ ባጣው ሃያል ስሟን፣
በጨለመ ተስፋ ጥጋ-ጥጉን ሳስስ
እግር ጣለኝና ከምታቃስት ነፍስ፣
ደሟንም ተመጣ
ሥጋዋን ተግጣ
ተሰብሮ አጥንቷ
መቅኔዋ ሲጠጣ፣
ባህያ ቆዳ ላይ ተንጋላ ተኝታ
አየኋት ሀገሬን በቀን ጅብ ተበልታ።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ
በጣም አዲስ ልጥፍ
የቆየ ልጥፍ
መነሻ
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
አስተያየቶች ለጥፍ (Atom)
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ