እሑድ 30 ማርች 2014

ተበልታ

 ተደግፋ ባጥንት
ተመርጋ በሥጋ
ተለስና በደም፣
እንቡጦቿን ቀጥፋ
ክፉ ዘመን አልፋ
ደብዛዋ ቢጠፋ፣
በየአደባባዩ ስፈልግ ስማስን
በደግ ሲነሳ ባጣው ሃያል ስሟን፣
በጨለመ ተስፋ ጥጋ-ጥጉን ሳስስ
እግር ጣለኝና ከምታቃስት ነፍስ፣
ደሟንም ተመጣ
ሥጋዋን ተግጣ
ተሰብሮ  አጥንቷ
መቅኔዋ ሲጠጣ፣
ባህያ ቆዳ ላይ ተንጋላ ተኝታ
አየኋት ሀገሬን በቀን ጅብ ተበልታ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ