ረቡዕ 19 ማርች 2014

ባህር ላይ ስራመድ

ዋናተኛው መንጋ
ሲንሳፈፍ ከታች ላይ፣
እኔ ግን ብቸኛው
ስራመድ ባህሩ ላይ፣
ለዚህ አይነት ጥበብ
አልደረሰም ብለው፣
ያዩትን ጥሬ ሀቅ
ወደጎን ትተው፣
ከቁብም ሳይቆጥሩኝ
አለፉኝ ናቅ አርገው።

እኔ ግን ብቸኛው
በሰፊው ባህር ላይ፣
ሲሻኝ ተቀምጬ
ኑሮን ሳሰላስል፣
ሲለኝ ተነስቼ
ስራመድ ያለእክል፣
ዋናተኛው መንጋ
ሰማሁት እንዲህ ሲል፣
"በዚህ በባህር ላይ ቆሞ 'ሚራመደው
እንደኛ ተንሳፎ መዋኘት ከብዶት ነው"።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ