ሰኞ 17 ማርች 2014

መኖር

መኖር፣
ያለፈውን ፅልመት፣
ማህደሩን ዘግቶ።
መኖር፣
ባለው በቀረው ላይ፣
የተስፋ ዘር ዘርቶ።
መኖር፣
ከፊት ለሚመጣው፣
ቅን ልቦናን ከፍቶ።
አለበለዚያማ.......
ነገር-አለሙን ካከረርነው'ማ
ብንወጣት ብንወርዳት፣
ይህቺን ረቂቅ ዓለም
የጀመራት - ሁሉም፣
የጨረሳት - ማንም!

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ