የብርሃኑ ስንኞች
የስነ-ግጥም ጦማር
Home
About
ማክሰኞ 1 ኤፕሪል 2014
እነርሱ ለእርሱ
ያረገዝውን እያማጡ
ያማጠውን እየወለዱ
የወለደውን እየሳሙ
ያሳደገውን እየዳሩ
የሞተበትን እየቀበሩ
ሙት-አመት እየዘከሩ
በምስለ-እርሱ ሲኖሩ፣
እርሱ ሲፈልግ እርሱን
ስጋው ቢሸኛት ነፍሱን፣
ያልሆናቸው ግን የሆኑት
ጨክነው ሜዳ ላይ ሳይጥሉት፣
በእልፍ ፍራንክ በተገዛ
በተሰራ ከርጥብ ዋንዛ
በልኩ ጎጆ ቀለሱና
ያፈር ካባ ደረቡና
አስሸለቡት ላይል ቀና።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ
በጣም አዲስ ልጥፍ
የቆየ ልጥፍ
መነሻ
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
አስተያየቶች ለጥፍ (Atom)
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ