እሑድ 13 ኤፕሪል 2014

ምነዋ ጣይቱ?

ፍጥረት አይኑን ገልጦ
ግራ ቀኙን ቃኝቶ
ተንጠራርቶ ተጠራርቶ፣
ምድር ፊቷን አፍክታ
ቆፈኗን በጮራ ተክታ፣
ምኞት ከተስፋ ሰንቆ
አንጀቱን ቋጥሮ አጥብቆ፣
ዱር ገደሉን ሊያቀና
ወገን ባለ ደፋ-ቀና፣
ባንቺ በጣይ'ቱ
በብርሃን ለጋሲ'ቱ፣
ስታሞቂን በፈገግን
ስታበስይን በሞከክን
እያረርንም እንደሳቅን
እያከሰልሽ አሳመድሽን።
ግን ለምን ጣይ'ቱ?!
ብርሃን ለጋሲ'ቱ!
አንፀባራቂ'ቱ!

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ