ረቡዕ 9 ኤፕሪል 2014

መጥዋቹ

አዛኝ የሚመስለው
ከንፈር የሚመጠው
የፀዳ የነጣ ኩታ የሚለብሰው
ለጥድቅ እጅ መንሻ እጁ የሚፈታው ፣
ይሄ እልፍ አሕዛብ ይሄ እልፍ አማኝ
የሚርመሰመሰው ባለፍኩ ባገደምኩኝ
ቤሳ ሲጥል እንጂ ሲሰጥ አላየሁኝ።

NB: Inspired by Bewketu Seyoum's "The road to nowhere" on Modern Poetry in Translation

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ