የብርሃኑ ስንኞች
የስነ-ግጥም ጦማር
Home
About
ማክሰኞ 29 ኤፕሪል 2014
ሰሚ ማጣት
አንገቴ አይል ቀና ፣ እንዳምናው ዘንድሮ፤
በደም መጣጭ ተባይ ፣ ጫንቃዬ ተወሮ።
ከላዬ አሽቀንጥሬ ፣ አላፈርጠው ነገር፤
እጄ ተጠፍሯል ፣ ግራው ከቀኙ ጋር።
እንዳልደባልቀው ፣ መንደሩን በሩምታ፤
ልጉሙ ልሳኔ ፣ ነጥፏል ለኡኡታ።
የጆሮ ኩሊ እንጂ ፣ ሰሚ በሌለበት፤
በግፍ አዳራሽ ዉስጥ ፣ ጥግ ይዤ በትዝብት፤
በዝምታዬ ፍም ፣ አቀልጣለሁ ጩኸት።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ
በጣም አዲስ ልጥፍ
የቆየ ልጥፍ
መነሻ
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
አስተያየቶች ለጥፍ (Atom)
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ