ሐሙስ 3 ኤፕሪል 2014

የግጥም-ጥም

በምናብ መገለጥ ተጋግሮ
በብርሃን ሰይፍ ካልተቆረሰ፣

በፅናት መቀነት ጠብቆ
ባንጀት ካንጀት ካልተቋጠረ፣

በመራር ያሞት ከረጢት
በእውነት ካልተሰተረ፣

በሃሳብ እንዝርት ሹሮ
በስሜት ቀመር ተዳውሮ
በተቡ ቃላት ካልተሸመነ፣

በዉበት ጥለት ተቋጭቶ
በሕብረ-ቀለም ካልተሸለመ...

ካንገት በላይ ተጠምቆ
ቅራሪ ስንኝ ቢቀዳም፣
ምላስን ከማራስ አልፎ
የግጥምን ጥም አይቆርጥም።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ