ሰኞ 21 ኤፕሪል 2014

ገዥና ሻጭ

የጥንቱ ነጋዴ ፣ ስንፍናው ላሳር ነው፤
መሸጥ አይችልበት ፣ መግዛት ካባቱ ነው።
የዘመኑ ጮሌ ፣ ብልጥ ነው ጨላጣ፤
መግዛቱ ሳያንሰው ፣ በንጣቂ ረብጣ፤
አንደ'ዜ በጥቅል ፣ ሌላ'ዜ ቆንጥሮ፤
ባ'ራጣ ይሸጣል ፣ ወለድ ተደራድሮ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ